Friday, November 30, 2012

በመሪዎቻችን ላይ የተመሰረተው ህገ ወጥ ክስ ህዝብን የማሸበር አይነተኛ መገለጫ ነው!!

በመሪዎቻችን ላይ የተመሰረተው ህገ ወጥ ክስ ህዝብን የማሸበር አይነተኛ መገለጫ ነው!!

እነሆ በሀይማኖታችን ላይ የተፈፀሙብንን የመብት ጥሰቶች በግላጭ ወጥተን ‹‹የፍትህ ያለህ›› ስንል 11 የተቃውሞ ወራት አለፉ፡፡ በእዚህ ሁሉ ግዚያት የሙስሊሙ ህብረተሰብ እጅግ አስደማሚ የሰላማዊ ትግልን ባህል በአንድ በኩል በሁሉም ህብረተሰብ ዘንድ ሰርፆ እንዲገባ ያስቻለ ሲሆን በሌላ በኩል መንግስት በተከተለው እጅግ የተወላገደ አረዳድ የወሰዳቸው ሀላፊነት የጎደለው እርምጃዎች ከህዝብ ልብ ከነ አካቴው እንዲወጣ ከፍተኛውን ሚና እየተጫወተ ይገኛል፡፡

ህዳር 21 የጀርመን ሬዲዩ የዘገበው ዘገባ ሰለ ኮሚቴዎቻችን



የአቃቤ ሕግን የመቃወሚያ ምላሽ ለመስማት ቀጠሮ ሰጥቶ የነበረው ፍ/ቤት ለሚቀጥለው ሳምንት ኅዳር 27 ቀጠሮ ሰጥቷል፡፡ የችሎቱን ውሎ ቆየት ብለን እናቀርባለን፡፡ በአካባቢው የምንገኝ ሁሉ መሪዎቻችን ጊቢውን ሲለቁ እኛም ወደየአካባቢያችን እንበተናለን፡፡

 ድምፃችን ይሰማ


ታሳሪዎቹ ከመንግስት ጋር በአንድ ጠረፔዛ ተቀምጠው ሲወያዩ የነበሩ ናቸው

“ታሳሪዎቹ ከመንግስት ጋር በአንድ ጠረፔዛ ተቀምጠው ሲወያዩ የነበሩ ናቸው” አቶ ተማም አባ ቡልጉ የኮሚቴዎቹ ዋና ጠበቃ ትላንት ማክሰኞ በወጣችው ኢትዮ ምህዳር ጋዜጣ ላይ የሰጡት ሙሉ ቃለ መጠይቅ፡፡
ኢትዮ -ምህዳር :- ሃሙስ ህዳር 13\2005 የኢትዮፕያ ሙስሊም ማህበረሰብ ችግሮች መፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴ አባላት በከፍተኛው ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 4ኛ ወንጀል ችሎት የጊዜ ቀጠሮ ነበራቸው የችሎቱ ውሎ እንዴት ነበር ?
ተማም አባ ቡልጉ :- በእለቱ ደንበኞቻችን ላይ የቀረበው ክስ ተነቧል፡፡ 23 ገፅ ክስ ነው፡፡ ዐቃቤ ህግ ያቀረበው ክስ የመጀመሪያው የፍርድ ቤት ቀነ ቀጠሮ ክሱና ማስረጃ ተብሎ የቀረበው ሰነድ ብዙ ስለነበር በአግባቡ ለይተን እንድንመጣ 19 ቀን ፍርድ ቤቱ ቀጠሮ ሰጥቶን ስለነበር እሱን ለይተን የክስ መቃወሚያ በንባብ አቀረብን፡፡ ዐቃቤ ህግ የመቃወሚያ መቃወሚያ ለማቅረብ ለመጪው አርብ ቀነ ቀጠሮ ተሰጥቶናል፡፡

Wednesday, November 28, 2012

አገር በሀሰተኛ የሰልፍ ድራማ አትመራም፡፡



ዛሬ በገርባ ከተማ መንግስት የግዳጅ ሰልፍ ማስወጣቱ ተሰማ


በአማራ ክልል በደቡብ ወሎ ዞን በገርባ ከተማ መንግስት የአካባቢውን ህዝብ በማስገደድ ዛሬ ሰልፍ ሲያስወጣ ውሏል፡፡ በሰልፉ ላይ ህዝቡ እንዲሳተፍ የአካባቢው ሹማምንትና ካድሬዎች ማስፈራሪያ የታከለባቸው ከፍተኛ የቤት ለቤት ቅስቀሳዎች ሲያካሄዱ የከረሙ ቢሆንም፤ መንግስት የሰልፈኛው ቁጥር ጥቂት ይሆናል በሚል ሥጋት ሰልፉ የሚካሄድበትን ቀን የከተማዋ የገበያ ቀን እንዲሆን በማድረግ፤ ለገበያ የወጣውን ህዝብ በማስገደድ ወደ ሰልፉ እንዲጓዝ አድርጓል፡፡ መንግስት ለሚዲያ ፕሮፖጋንዳ ፍጆታ እንዲመቸው በማድረግ ህዝቡን ‹‹አክራሪነትን እንቃወማለን፣ በሃይማኖት ሽፋን አድርገው የግል የፖለቲካ አጀንዳቸውን ለማሳካት የሚንቀሳቀሱ ሃይሎችን እንቃወማለን፣ መንግስት በመላ ሃገሪቱ አክራሪነትን እና ሽብርተኝነትን ለማጥፋት እየወሰደ ያለውን እርምጃ እንደግፋለን፣ በከተማችን መንግስት አክራሪዎች ላይ እየወሰደው እርምጃ ተገቢ ነው፣ የጀመርነው ልማት በአክራሪዎች አይደናቀፍም›› የሚሉ እና በከተማው አስተዳደር የተዘጋጁ መፈክሮችን በእጁ እንዲይዝና በተደጋጋሚም በድምጹ እንዲያሰማ ሲያስገድዱት ውለዋል፡፡

Monday, November 26, 2012

በመሪዎቻችን ላይ የተመሰረተው ህገ ወጥ ክስ ህዝብን የማሸበር አይነተኛ መገለጫ ነው!!


በመሪዎቻችን ላይ የተመሰረተው ህገ ወጥ ክስ ህዝብን የማሸበር አይነተኛ መገለጫ ነው!!

እነሆ በሀይማኖታችን ላይ የተፈፀሙብንን የመብት ጥሰቶች በግላጭ ወጥተን ‹‹የፍትህ ያለህ›› ስንል 11 የተቃውሞ ወራት አለፉ፡፡ በእዚህ ሁሉ ግዚያት የሙስሊሙ ህብረተሰብ እጅግ አስደማሚ የሰላማዊ ትግልን ባህል በአንድ በኩል በሁሉም ህብረተሰብ ዘንድ ሰርፆ እንዲገባ ያስቻለ ሲሆን በሌላ በኩል መንግስት በተከተለው እጅግ የተወላገደ አረዳድ የወሰዳቸው ሀላፊነት የጎደለው እርምጃዎች ከህዝብ ልብ ከነ አካቴው እንዲወጣ ከፍተኛውን ሚና እየተጫወተ ይገኛል፡፡

Sunday, November 25, 2012

አባይና የኢትዩጲያ ሙስሊም

አባይና የኢትዩጲያ ሙስሊም

(በኢትዮ-አልሀበሺ)
መቼም የአባ ጉዳይ የኢትዩጲያና የተፋሰሱ ሀገራት የልብ ትርታ መሆን ከጀመረ ዘመናት አልፈዋል፡፡ የአባይ ግድብ ጉዳይ ደግሞ ትርታውን በይዘትም በፍጥነትም አሙቆታል፡፡ የምስራቅ አፍሪካን ፖለቲካ በቅርብ የሚከታተሉ የዘርፉ ምሁራን ሠላማዊ የመሠለው የአባይ ግድብ ግንባታ ሂደት እንደሚታሠበው አልያም እንዲታሠብ እንደተፈለገው ፍፁም ሠላማዊ እንዳልሆነ መግለፅ ጀምረዋል፡፡ ከባቢውም ከአደጋ አልፀዳም፤ እንደውም የቁርሾ እና በጎሪጥ የመተያየት ጉም ማንዣበብ ስለመጀመሩ አንዳንድ ምልክቶች እየተስተዋሉ እንደሆነ አሁን አሁን መረጃዎች እየወጡ ነው፡፡ በሌላ በኩል የኢትዩጲያን ፖለቲካና ወቅታዊ የሙስሊሞችን ጉዳይ ካሠብነው በላይ ሠፋ ባለ መልኩ የቃኘው የቀድሞ የኢህአዴግ አባል አብደላህ አደም ተኪ ዝርዝር ፅሁፍም በተወሠነ መልኩ ከመጋረጃው ጀርባ ያሉ ድብቅ ተልዕኮዎችን ዳሷል፡፡ የመለስ ኢትዩጲያ (እዚህ ላይ እኛ በሀገርነቷ የምንኮራባት፤ እትብታችንን የቀበርንባት እና ልንዋደቅላት ተፈጥሮአዊ ቃልኪዳን የገባንላት ውዷ ኢትዩጲያችን ሳትሆን፡ የእግር እሳት ሆና ዕምነታችሁን ቀይሩ እስከማለት የዘመተችብንን ኢትዩጲያ ለመግባባት ያክል “የመለስ ኢትዩጲያ” ለማለት መርጫለሁ፡፡) አህባሽን ለማጥመቅ ስትሠናዳ እና በህዝብ የተተፋውን የኤልያስ REDMAN መጅሊስ ለህዝብ ያሠቡ በማስመሠል እጅግ በተጠና መልኩ ማንነታቸው የማይታወቅ፤ ሲያዩአቸው ግን እስላማዊ ቁመና ያላቸው የሚመስሉ አህባሽ አመራሮችን ከያሉበት ለቅመው በሲስተም ሲያሰርጉ፡ ቀጣይ ጥንስሶችንም በአህመዲን አብዱላሂ ያልበሠለ ካቢኔ እንጭጭ አዕምሮ ሊታሰብ ከሚችለው በላይ በተጠና አኳኋን አላህ እስካጋለጠው ድረስ ውስጥ ውስጡን ማስፈፀም የጀመሩበት አካሄድ እንደሚታሠበው ከአንድ እና ሁለት ሠው ውሳኔ የዘለለ ውስብስብ የፖለቲካ ሴራ ነበር፡፡

Saturday, November 24, 2012

በሽብርተኝነት የተከሰሱ 29 ተጠርጣሪዎች በነፃ እንዲሰናበቱ ተጠየቀ

-    የተከሰሱበት ሕግ ለትርጉም ለፌዴሬሽን ምክር ቤት ይላክ ተባለ
-    የአቶ ጁነዲን ሳዶ ባለቤት ክስ ተለይቶ እንዲቀርብ ተጠይቋል

በታምሩ ጽጌ (reporter)
የሽብር ድርጊቶችን በመፈጸም፣ ሕገ መንግሥቱንና መንግሥታዊ ሥርዓቱን በማፈራረስ ሙከራ ወንጀልና ለሽብርተኝነት ድጋፍ በመስጠት ወንጀል ተጠርጥረው በፌዴራል ዓቃቤ ሕግ ክስ የተመሠረተባቸው 29 ግለሰቦችና ሁለት ድርጅቶች፣ የተከሰሱት ሕገ መንግሥቱን ጥሶ በወጣ ወይም በሚቃረን ሕግ በመሆኑ በነፃ እንዲሰናበቱ ጠበቆቻቸው ጠየቁ፡፡ ከሚኒስትር ጁነዲን ሳዶ ባለቤት ተጠርጣሪ ወይዘሮ ሐቢባ መሐመድ መሐሙድ በስተቀር፣ ሁሉም ተጠርጣሪዎች በጋራ አሥር ጠበቆችን ያቆሙ ሲሆን፣ ክሱን እየመረመረው ለሚገኘው የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ አራተኛ የወንጀል ችሎት የክስ መቃወሚያ ሐሳባቸውን ኅዳር 13 ቀን 2005 ዓ.ም. አቅርበዋል፡፡

Friday, November 23, 2012

Lawyers: Terror Case Against 29 Ethiopians Faulty - ABC News

Lawyers: Terror Case Against 29 Ethiopians Faulty - ABC News
Defense lawyers have told the Ethiopian High Federal Court that terrorism charges against 29 Muslims are unconstitutional.
Federal prosecutors are accusing the 29, which includes prominent clerics, journalists and activists, with terrorism and attempts to create an Islamic state. Tensions have been rising between the government in this mostly Christian country and Muslim worshippers that have led to anti-government protests.
On Thursday one of the defense lawyers for the 29 said that they expect the court to throw the case out. The court will decide on Nov. 30 if it has jurisdiction over the case and whether the charges, partly based on the country's controversial anti-terrorism law, is constitutional.
Rights groups say the Ethiopian government provoked the protests by trying to impose a specific interpretation of Islam.

Thursday, November 22, 2012

የዛሬው ይፍርድ ቤት ውሎ የእኔ እይታ

የዛሬው ይፍርድ ቤት ውሎ የእኔ እይታ
ፍርድ ቤት የደረስኩት ከጧቱ አራት ሰዓት ላይ ነበር እኔ ስደርስ ፖሊስ ሙስሊሙን በሁለት ቦታዎች ከፍሎ ነበር (ፍርድ ቤቱ ውስጥ በረካታ ሙስሊም እነደነበረ የተጠበቀ ሆኖ) ከፍርድቤቱ በላይ በኩል ወደ ቤ/ክርስቲያን አቅጣጫ እንዲሁም በሌላው አቅጣጫ ወደ ህንፃ ኩሌጁ ….በሁለቱም ሙስሊም ስብስቦች መሃከል ፍርድቤቱ (ፍርድ ቤት ውስጥ በርካታ ሙስሊሞች እንደነበሩ ለመመልከት ችያለሁኝ) እንዲሁም በርካታ ፖሊሶች ይገኛሉ በፍርድቤቱ አከባቢ የሚገኙ ካፌና ሱቆች ግማሹን ሲያዘጉ እንዲሁም ክፍት የሆኑትን በር ላይ በመቆም ሙስሊም የሚመስለው እንዳይገባ ሲከለክሉ ተመልክቻለሁኝ፣ እኔም ሁለተኛውን ስብስብ ተቀላቀልኩኝ፣ ጥቂትም ሳልቆይ ህዝበ ሙስሊሙን ሲገፉ እና ሲያባርሩ የነበሩ ህግ አስከባሪ ተብይዎች ነገር ግን ህጉን በአግባቡ ያማያውቁት ፖሊሶች ተሰባስበን ካለንበት ቦታ አሁንም ወደ ኃላ እንድናፈገፍግ ጫና መፍጠራቸውን አላቆሙም ህዝበ ሙስሊሙ ግን በተረጋጋ ሁኔታ ከፖሊሶች ጋር መነጋገሩን ቀጥሏል.. ለምንድን ነው ቦታችንን ትተን እንድንሄድ የምታደርጉን የሚል ጥያቄውን እያቀረበ ቢሆንም ፖሊሶቹ ሊሰሙ አልፈለጉም በዚህ ግዜ ሙስሊሙ አሁንም በተረጋጋ ሁኔታ መንገድ ዘጋቹ ካላችሁን ይሄው መንገድ እንክፈት ከዚህ ውጭ ግን አንበተንም የመጣነው የኮሚቴዎቻችንን የፍርድ ሂደት ለመከታተል ነው ስለዚህ እዝህ ቆመን እንጠብቃለን በማለት መልስ ሰጠ፣ ሆኖም አሁንም ግን ፖሊሶች እንደውም ቆጣ ባለ መልኩ በቃ እናንተ አታስፈልጉም ይሄን ቦታ ለቃችሁ ተበተኑ ስብስባችሁን አንፈልግም በማለት በዱላ ለመማታት ይቃጣቸው ገባ በዚህ ወቅት አንዲት እህታችን እንባዋን እየዘረገፈች የሚከተለውን ንግግር ተናገረች “ለምንድን ነው እንደዚህ የምታመናጭቁን እኛ ኢትዮፕያዊ አይደለንም? ዜጋ አይደለንም? ብላ አምርራ አለቀሰች ይህን ግዜ የተወሰኑ ፖሊሶች ደንገጥ አሉ እና ውጥረቱን ረገብ አደረጉት ሆኖም ከፖሊሶች መሃከል አንድ ወጣት እና ቀጠን ያለ ቆጣ በተሞላበት ንግግር ተበተኑ ብሎ ለማስፈራራት ሙከራ አድርጓል ይህ ፖሊስ በጣም በሚገርም ሁኔታ ረመዳን 2 ላይ በአንዋር መስጂድ ላይ ፖሊስ ጥቃት በፈፀመ ግዜ ግንባር ቀደም በመሆን ሙስሊሙን በዱላ ሲቀጠቅጥ የነበረ ከመሆኑ በላይ በወቅቱ እኔም በጥላቻ የተሞላውን ዱላውን ቀምሻለሁኝ አላህ ያዋርደውና የተረገመ ሰው ነው ሆኖም ቁጭቴን በውስጤ ዋጥ አደረኩኝ፣ በዚህ ሁኔታ ባለንበት ወቅት ፖሊሶች ላይ መሰላቸት የተፈጠረ መሰለኝ ካስቆሙን ቦታ እንዳናልፍ ከፊት ለፊታችን ሆነው መከላከሉን ብቻ ማከናወን ያዙ እንዲሁም ከጦርሃይሎች አከባቢ የሚመጡ መኪኖች ወደፍርድ ቤቱ መንገድ እንዳይጠቀሙ ከለከሉ ሆኖም ግን ከላይ ከሜክሲኩ የሚመጡ መኪኖች ግን ያልፉ ነበር ብዙዎች ግራ በመጋባት በመስኮት ሲመለከቱ አስተውያለሁኝ፣ ይህ በእንዲህ እንዳለ ከፍርድቤቱ በር አከባቢ አንድ አውቶቢስ በሩ ተከፍቶ ሰዎች ሲገቡ ተመለከትን ግማሹ በአውቶቢሱ እየገቡ ያሉት ኩሜቴዎቻችን ሳይሆኑ አይቀርም የሚል ግምት ሳይወሰድ አልቀርም ፣ሁሉም በርቀት ለመመልከት መንጠራራት ጀመረ ይህ ሁኔታም ሁሉም በአንድነት አውቶቢሱን መመልከቱን ተያያዘ መኪናው ከእኛ ትንሽ ራቅ ያለ መሆኑና መኪናው ወደ ፍርድ ቤቱ በር የተጠጋ በመሆኑ የሚገቡትን ሰዎች መለየት አልተቻለም ሆኖም ግን በዚህ ወቅት ሁሉም ኮሚቴዎቻችን ናቸው በሚል እጅን ማውለብለቡን ተያይዞታል ቀስ በቀስ ሰው ስሜት ውስጥ ገባ በድንገት ሳይታወቅ ፌት ለፊት የነበሩትን ፖሊሶች በማለፍ ወደ ፊት መጠጋጋት ጀመረ ሁሉም ስሜት ውስጥ ገባ ግማሹ ያለቅሳል የተወሰነው ተክቢራ እያለ ነው ሌላው ያጨበጭባል በቃ ለጥቂት ደቂቃ ቢሆንም ድብልቅልቁ ወጣ ዋናው መንገድ ሙሉለሙሉ በሙስሊሙ ተዘጋ፣ አውቶቢሱም ነጎደ ከዛ ሰው መረጋጋት ጀመረ ፖሊሶቹ የህዝቡ ስሜት ሲመለከቱ ግራ ተጋብተው ታይተዋል በሂደት ግን ሰው ቀዝቀዝ ማለት ሲጀምር ሌላ ወሬ መወራት ጀመረ አሁን ያለፈው ባስ ኮሜቴዎቻችን የያዘው አይደለም የሚል ህዝቡም ተናደደ ሆኖም በተፈጠረው ግርግር ምክንያት ፌድራል ፖሊሶች ከላይ እየሮጡ መጡ የተወሰኑ ወንድሞችና እህቶችንም በዱላ መማታት ተያይዙት ይህ ሁኔታ ደግሞ የበለጠ ውጥረት ፈጠረ፣ ሆኖም የሰላም አምባሳደር የሆነው ሙስሊሙ ጥረት ነገሮች መረጋጋት ጀመሩ ሆኖም ግን ሁልግዜ ሁከት የሚፈልጉ ሰላም አደፍራሽ የሆኑት ደህነት ተብዪዎች ይህን አጋጣሚ በመጠቀም መርዛቸውን መርጨት ጀመሩ በሙስሊሙ መሃል ገብተው ግርግር ፈጠሩ ከዛም አልፈው ደደብ የሆኑት ደህንነት ተብዪዎች በማዘናጋት የተወሰኑ ሙስሊሞቹን ጠልፎ ለመውሰድ ሙከራ አደረጉ በዚህ ግዜ ሙስሊሙ ነቅቶባቸው ሊጠለፉ የነበሩትን ሙስሊሞች ማስጣል ተቻለ ሆኖም ግን ደህንነቱ ባሳየው ያልተገባ ባህሪ ምክያት ትንሽ ግርግር ተፈጠረ ድህነነቱም ሙስሊሙ ስሜት ውስጥ በመግባቱ ትንሽ ኩርኩም ቀመሰ ተደናግጦም በሩጫ ወደ ጓደኞቹ ተቀላቀለ ከዛም ጉዳት እንደደረሰበት በማስመሰል በደህንነት እና በፖሊሶች ታጅቦ ወደ ሙስሊሙ በመምጣት ለማስፈራራትና ለማስረበሽ ሙከራ ቢያደርጉም ሙስሊሙ በተረጋጋ መንፈስ ሁኔታውን አሳልፎታል ከዛ በመቀጠል የተወሰነ ቆይታ የተደረገ ሲሆን ኩሚቴዎች ሳይሄዱ አይቀርም የሚል መላ ምት በማመዘኑ 6፡25 አከባቢ ሙስሊሙ የተወሰነው ወደ ጦርሃይሎች አቅጣጫ ሴሄድ አብዛኛው ግን በጀመዓ ወደ ኮካ መስጅድ ሄዷል እሰከ 6፡35 ድረስ ግን ከጦርሃይሎች አቅጣጫ የሚመጣው የመኪና መንገድ ዝግ ነበር፣ ወደ 6፡40 አከባቢ ሁኔታውን በጥንቃቄ ስቃኝ ነበረ ሲሆን የተወሰኑ ወንድሞች ፍርድ ቤቱ አከባቢ በፖሊስ መኪና ተጭነው እንደነበር ለመመልከት ችያለሁኝ ሆኑም የመጨራሻውን ክስተት ለመመልከት አልታደልኩም፡፡ በመጨረሻም በዛሬው በነበረው ህዝበ ሙስሊም በጣም ኮርቻለሁኝ ወላሂ ለአላህ ብለን ለኩሚቴዎቻችን ያለንን ታማኝነት ነው ያሳየነው ወያኔ ግራ እንደገባው ተመልክቻለሁኝ፣ ለዚህም ነው ለሌላ ግዜ ተበሳጭተንና ተስፋ ቆርጠን እንድንቀር በማሰብ ይመስላል ሲያዋክቡን የነበረው በመሆኑም በቀጣይ በሚኖረው የፍርድ ሂደት ላይ የአሚሮቻችን ትእዛዝ በመጠበቅ መገኘት ይኖርብናል ሌላው አንዳንድ ወንድሞች ትንሽ ስሜት ውስጥ የመግባት ነገር ነበር እና ሰብር ይኑረን የወያኔ አላማ ሁከት መፍጠር ነው ብልጥ እንሁን ሌላው በአካል ባለውቃትም እንባዋን እየዘራች ለፖሊሶቹ ልክልካቸውን የነገርሽ እህቴ ጀዛኪላህ እኔ ያዩሁት ይህ ነበር እናንተ ይምትጨምሩትን እስቲ አካፍሉን 

ወንድማችሁ አማን

Tuesday, November 20, 2012

A Must Watch Video !! TPLFites are being Terrified!


በምስራቅ ኢትዮጲያ በኦጋዴን አከባቢ የፌደራል ፖሊስ አባላትን ሰብስበው ገለፃ ያደረጉት የፌደራል ፖሊስ ሃላፊ ፖሊሶች እየከዱ ማስቸገራቸውን ገልፀዋል። ለሰባት ዓመታት ለማገልገል የገቡትን ሥምምነት ጥሰው በመኮብለላቸው እየያዝን ጅጅጋ እስር ቤት እንከታቸዋለን ሲሉ አሳስበዋል። በምስራቅ ካለው ይልቅ የሰሜኑ ችግር የሰፋ መሆኑን በሁመራና በመተማ ዘወትር ግጭት በመታየት ላይ መሆኑን አብራርተዋል።
በደቡብ ወሎ ሙስሊም መሆን ወንጀል ሆኗል!

መንግስት ምን እየሰራ ነው?

የኢህአዴግ መንግስት ‹‹አክራሪነትን ለመግታት›› በሚል የሀሰት ምክንያት የአህባሽን አንጃ በሙስሊሙ ህብረተሰብ ላይ ለመጫን ሙከራ ማድረግ ከጀመረበት ካለፈው አመት ጀምሮ ታላቅ ብሄራዊ ተቃውሞ እንደገጠመው ይታወቃል፡፡ ህዝበ ሙስሊሙ ‹‹ዲኔን አላስነካም›› በሚል ስሜት የተሰነዘረበትን ጥቃት ለመመከት ባደረገው እጅግ ሰላማዊ ትግልም በርካታ ድሎችን ሲጎናጸፍ ቆይቷል፤ መንግስትም በበኩሉ ሰላማዊውን ትግል ለማስቆም በወሰዳቸው ኢሰብአዊ እርምጃዎች ህዝበ ሙስሊሙ ይህ ነው የማይባል መስዋእትነትን ለመክፈል እንደተገደደው ሁሉ!

በዚሁ ታሪካዊ ሰላማዊ ትግል በከፍተኛ የተቆርቋሪነት ስሜት የመንግስትን ውስብስብ ሴራ መና ሲያስቀሩ ከነበሩ ጠንካራ ክልላዊ ተቃውሞዎች አንዱ በወሎ ክልል የነበረው ተጠቃሽ ነው፡፡ በተለይ በደቡብ ወሎ ክልል በሰደቃና በአንድነት ፕሮግራሞች የተደረገው ህዝባዊ ንቅናቄ እና የመጅሊሱን ምርጫ መና ያስቀረው የህዝብ አንድነት ያበሳጨው መንግስት የጭካኔ እርምጃዎችን ጭምር በመውሰድ ለማስቆም ጥረት አድርጓል፡፡ የደቡብ ወሎ እምብርት በሆነችው በደሴ ሙስሊሞች ላይ የተፈጸመው የፈደራል ፖሊሶች ጥቃት ሳይሽር የመንግስት የጸጥታ ሃይሎች በአካባቢው ባሉ ከተሞች ላይ የሚፈጽሙትን ህገ ወጥ ጥቃት ቀጥለዋል፡፡ ይህ የመንግስት ህገ ወጥ አካሄድ ከሞላ ጎደል ምን ይመስል እንደነበር በመጠኑ ለማየት እንሞክር፡፡

Monday, November 19, 2012

Jewish Rabbi says Islam is religion of future

ታላቁ ታሪካዊ የዚያራ ፕሮግራም በ ጀርመን ራዲዮ

High time to support Ethiopian Muslims

High time to support Ethiopian Muslims

by Abebe Gellaw
Ethiopian Muslims are waging their struggle in a religious contextFor the last two decades, nonviolent struggle, or civil resistance, appeared to be highly misunderstood and confused in Ethiopia. The resultant effect of this confusion is that so many opportune moments to build a movement for change have been wasted. In fact, a number of leaders failed to provide the necessary leadership to mobilize the oppressed people of Ethiopia to confront their oppressors.
Though Ethiopian Muslims are waging their struggle in a religious context, they are showing us that nonviolent struggle is not “impossible” but a “force more powerful” to crack, stress out and eventually dismantle the tyrannical TPLF regime. While the regime has left no stone unturned to isolate the struggle of Muslims through its confusing and divisive propaganda, the movement is gaining momentum and getting smarter. It now stands out that the movement has reached a critical stage. Despite its best efforts, TPLF has failed to put the genie back into the bottle as the movement has already become irrepressible.

የመራኑ ሃቢብቲ የቃሊቲ የዚያራ ትረካ



የመራኑ ሃቢብቲ የቃሊቲ የዚያራ ትረካ

"ስለፌዴራል ፖሊሶች ግን ባላወራ ይቀለኛል፡፡ ቅንነት የሚባል ነገር
አልፈጠረባቸውም፡፡ ህዝቡ የሚደናበር መስሏቸው እስከ አፍንጫቸው ታጥቀው በህዝቡ መሃል በመኪና አስሬ ይመላለሳሉ፡፡ ግብር ከፍሎ በሚያስተዳድራቸው ወንድሞቻቸው መሃል ሳይሆን በሃገሪቱ ላይ የሆነ የጠላት ጦር ወረራ ፈፅሞ ለግዳጅ የተሰማሩ ነበር የሚመስሉት፡፡ የአሜሪካን ጦር አባላት እጅግ በሚያስፈራው የአፍጋኒስታን የቶራ ቦራ ተራራ አካባቢ ሲሰማሩ እንኳ እንደዚህም የታጠቁ አይመስለኝም፡፡ ፌዴራል ፖሊሶቹ ክላሻቸውን ወደ ሰላማዊው ህዝብ ደግነው በፓትሮል ወዲህ ወዲያ ይላሉ፡፡ እብዛኛው የፌዴራል ፖሊሶቹ አባላት ከታጠቁት ትጥቅ በተጨማሪ ደረታቸውን ያሳበጠ የደረት መከላከያም አድርገዋል፡፡"

ቃሊቲ አቅሏን ሳተች
ወደዳችሁም ጠላችሁ ግርማ ሞገሱ ከሩቅ ይስባችኋል፡፡ በነጭ ጀለቢያ ተውቦ ፍፁም ርጋታ በተላበሰ ሁኔታ ሊዘይሩት የመጡትን ጠያቂዎች በአይኑም፣በፈገግታውም፣ ጭንቅላቱንም ጭምር በመነቅነቅ ምስጋናውን ይገልፃል፡፡ ይህ ሁኔታ ለረጅም ሰዐት የዘለቀ ቢሆንም እሱና ጓደኞቹ ያለምንም ድካም ጠያቂዎቻቸውን(ዘያሪዎቻቸውን) ተቀብለው እያስተናገዱ ነው፡፡ ጠያቂዎችም ያለምንም ፋታ መፍሰሳቸውን ቀጥለዋል፡፡ ልክ የአባይ ዉሃ አገር አቆራርጦ እየፈሰሰ ከግብፁ አስዋን ግድብ እንደሚጨመረው አይነት ጠያቂዎችም በረጅሙ እየፈሰሱ ከዚህ ቆፍጣናና ልበ ሙሉ ወጣት አጠገብ ሲደርሱ ከንግግግር ይልቅ እንባ ይተናነቃቸዋል፡፡ ይህ ወጣት በቅርቡ ወደዚህች አለም ከመጣች ሳምንት ያልሆናት የሱመያ አባት የሆነው አህመዲን ጀበል ነበር፡፡
ውድ አንባቢያን ከሰላምታዬ አስቀድሜ በቀጥታ ወደቃሊቲ እስር ቤት ያስገባሁህ ወድጄ እንዳይመስልህ ናፍቆት ነበረብኝና ነው፡፡ የቃሊቲ ትርክቴን ያቋረጥኩት የአንተን ልብ ለማንጠልጠልም አይደለም፡፡እመለሳለሁ፡፡ ናፍቆቴን ላጣጥም ብዬ እንጂ፡፡

Sunday, November 18, 2012

ትግሉ ዛሬም በሌላ ምዕራፍ ላይ ነው፡፡

ድምፃችን ይሰማ
የዛሬው የዚያራ መርሐ ግብር ሪፖርታዥ

ትግሉ ዛሬም በሌላ ምዕራፍ ላይ ነው፡፡

ዛሬ በስኬት የተጠናቀቀው የጉዞ ቃሊቲ የዚያራ መርሐ ግብራችን ይፋ ከተደረገበት ሐሙስ ምሽት ጀምሮ ነበር በርካታ ሕዝብ ሂደቱን በስኬት ጀምሮ በስኬት ለማጠናቀቅ ቅድመ ዝግጅት ማድረግ የጀመረው፡፡ በሁሉም አካባቢዎች በተደረገው የተቀናጀ አንቅስቃሴ ሁሉንም መዳረሻ መንገዶች ያካተተ ሰፊ የቅስቀሳ ስራ ተሰርቷል፡፡ በመርሐ ግብሩ እቅድ ላይ መንግስት ያሰማራቸው አካላት ትእይንተ ዚያራውን ወደ ሌላ አቅጣጫ ሊለውጡት ይችሉ ይሆናል የሚል ስጋት የነበረ ቢሆንም ሙስሊሙ ኅብረተሰብ ባካበተው እና ከዚህ ቀደምም በተደጋጋሚ ባሳያቸው ሰላምን እሰከመጨረሻው የመጠበቅ
ስልት በመተማመን መርሐ ግብሩ በታቀደለት መልኩ ሊሄድ ችሏል፡፡

 
በበርካታ አካባቢዎች የሚኖሩ ሙስሊሞች የቃሊቲ ጉዞአቸውን የጀመሩት ገና ከሌሊቱ 11፡30 ጀምሮ ነበር፡፡ እለቱ እሁድ በመሆኑ ችግሩን አቃለለው እንጂ በሕዝቡ ብዛት የተነሳ ከፍተኛ የትራንስፖርት ችግር ገና ከማለዳው ጀምሮ ተፈጥሮ ነበር፡፡ ሆኖም የተገኘውን የግልም ሆነ የሕዝብ ትራንስፖርት እንዲሁም በእግርም ጭምር በመጓዝ ቃሊቲ የደረሰው ሕዝበ ሙስሊም በደቂቃዎች ጊዜ ነበር የአካባቢውን ነፋስ የለወጠው፡፡ ቃሊቲ በውስጡ እንደያዛቸው ንጹሐን መሪዎቻችን እና ‹‹እንደ ሕዝብ ታስረናል›› የሚል መልዕክት በሚያስተላልፉ ሙስሊሞች ተሞላ፡፡ ቃሊቲና አካባቢው እየጠበበ፣ የሰው ቁጥር ግን እያየለ መጣ፡፡ የህዝቡ ወረፋ ሶስት ረድፍ ሰርቶ መንደሮችን እያቆራራጠ ነጎደ፡፡ ሳይታሰብ በጥቂት ደቂቃዎች ውስጥ የቃሊቲ አውራ ጎዳና አፋፍ ላይ ደረሰ፡፡ ‹‹ሰልፉ ወደ ጎዳና መውጣቱ ብዛቱን ያሳብቃል›› የሚል ስጋት የገባቸው የጸጥታ አካላት ሰልፉ ወደ ሌሎች አጎራባች መንደሮች እንዲቀጥል ቢያደርጉም መንደሮቹ እየሞሉ በርካታ ሕዝብ ዋናው ጎዳና ላይ ፈስሶ ታይቷል፡፡

ዘግይቶ ቢሆንም የማረሚያ ቤቱ በር ለጎብኚዎች ክፍት ሲደረግ ሙስሊሙ ኅብረተሰብ በተሠጠው መመሪያ መሰረት በእርጋታ ያለ ምንም ግፊያ ወደ ውስጥ መግባት ጀመረ፡፡ በማረሚያ ቤቱ የነበረው ፍተሻ ከወትሮው የተለየና ጫማን እስከማስወለቅ የደረሰ ነበር፡፡ ሕዝቡ በሌሊት ከቤቱ በመውጣትና ይሄንን አስቸጋሪ የቃሊቲ ረጀም መንገድ በመጓዝ (በአማካይ ለትራንስፖርት እስከ 12 ብር ድረስ በመክፈል) ለሰዓታትም በቃሊቲ በር ላይ ለመጠበቅ የተገደደው ሕዝብ ፍተሻውን አልፎ የናፈቃቸውን መሪዎች ሲያገኝ እንባውን መዝራት ይጀምራል፡፡ ሕጻን፣ አዋቂ፣ ሴት፣ ወንድ፣ ጎልማሳ፣ አረጋዊ ሳይል መሪዎቹን የሚቀበለው አንዳንዱ በለቅሶ፣ ሌላው ሀዘን ባጠላበት ፊት! የኅሊና እስረኞቹ መሪዎቻችን ዘወትር እንደሚደርጉት የሚያለቅሰውን ሕዝብ ከሽቦው አጥር ጀርባ ሆነው ያባብላሉ፡፡ ይህን ትእይንት የተመለከተ ታሳሪዎቹ ሕዝቡ እንጂ መሪዎቹ አይመስለውም፡፡ ለነገሩ ሕዝቡም በፍትህ እጦት ‹‹ኢትዮጵያ በምትባል ትልቅ እስር ቤት ታስሬያለሁ›› የሚል መልዕክት ለማስተላለፍም ጭምር ነበር የዚያራ ፕሮግራሙን ያካሄደው፡፡ ሕዝቡ ከኋላ ለተሰለፉት መቶ ሺዎች እድል ለመስጠት ሲል በመከራ ያገኘውን ቃሊቲ የመግባት እድል ለቅጽበት ያህል በመጠቀም ለተረኛው ሙስሊም ይሰጥ ነበር፡፡

የእድል ነገር ሆኖ ከኡስታዝ አህመድ ሙስጠፋና ጋዜጠኛ ዩሱፍ ጌታቸው በስተቀር ሁሉም የኅሊና እስረኞቻችን አንድ ላይ ነበሩ፡፡ ዞን ሶስት ላይ ተደርድረው የቆሙት ቀሪዎቹ 27 የኅሊና እስረኞች ከማለዳው ጀምሮ አስከ ቀትር ድረስ ያለምንም እረፍት ሊጎበኛቸው የመጣውን ሕዝብ ሲቀበሉ፣ ሲያበረታቱ፣ ሲመክሩ እና ዱአ ሲጠይቁ ውለዋል፡፡ ይህም ሆኖ ግን ሊዘይራቸው ከመጣው ሕዝብ እድሉን አግኝቶ በአይን የተያያቸው ሩብ ያህሉ እንኳ አይሞላም፡፡ የማለዳውን ብርድ እና የረፋዱን ጸሐይ ተቋቁሞ በትእግስት ሲጠብቅ የነበረው በቁጥር የሚበዛው ሙስሊም የመግባት እድሉን እንደማያገኝ እያወቀም ቢሆን የዚያራ ፕሮግራሙን ለማሳካት ሲል በሰልፍ ተሰድሮ ነበር፡፡ የሰልፉን ጫፍ ለማግኘት የዚህ ሪፖርታዥ አዘጋጆች ሰልፉን ተከትለው ቢጓዙም በሰልፉ ርዝማኔ የተነሳ ጫፉን ለማግኘት ሳይችሉ ቀርተዋል፡፡ ይሄ ሁሉ ሕዝብ ግን መሪዎቹንም ሆነ የመንግስትን ያልተገደበ ጣልቃ ገብነት አስመልክቶ ያለውን አቋም በማያሻሙ ቃላት ዛሬም በድጋሚ ለመንግስት በማረጋገጥ ወደ ቤቱ በሰላም መመለስ ጀምሯል፡፡

በሰላም ተጠናቅቋል ሲባል የነበረውን ሰላም ለማደፍረስ ጥረቶች አልተደረጉም ማለት አይደለም፡፡ ሰላማዊውን ሕዝብ ከማመናጨቅ አንስቶ የበርካታ ሙስሊሞችን የመኪና ታርጋ እስከ መፍታት የደረሰ ትንኮሳ በጸጥታ አካላትና በትራፊክ ፖሊሶች ተፈጽሟል፡፡ እስከ አፍንጫቸው የታጠቁ የፌዴራል ፖሊስ ኃይሎች በልዩ መለዮዋቸው ነገር ፍለጋ በሚመስል መልኩ ተደጋጋሚ ከበባ በተሸከርካሪዎች በመታገዝ በሙስሊሙ ላይ ቢያደርጉም ሕዝቡ ያለ ምንም መሳቀቅ ሙከራውን አክሽፎታል፡፡ በፕሮግራሙ ላይ ‹‹በሞባይል ሲቀርጹ ነበር›› የተባሉ 5 የሚደርሱ ወጣቶች በፖሊሶች ታፍነው ተወስደዋል፡፡ ይሄም የትንኮሳው አካል ነበር፡፡ ከዚህ በተጨማሪም ዚያራውን ጨርሰው ወደ ቤታቸው ይሄዱ የነበሩ ሙስሊሞች ሳሪስ ቀለበት መንገድ አካባቢ በፖሊስ ትንኮሳ ሲደረግባቸው የነበረ ቢሆንም ሁኔታውን ሕዝቡ በሰላም ለማሳለፍ ያደረገው ጥረት ተሳክቶ ያለምንም ችግር በሰላም ተጠናቅቋል፡፡

ለመርሐ ግብራችን ስኬት የሙስሊሙ መኅበረሰብ ሰላም ወዳድነት አብዩን ሚና የተጫወተ ቢሆንም የሌላ እምነት ተከታዮች በተለይም ክርስቲያን ወገኖቻችን ዚያራው በሰላም እንዲጠናቀቅ ሁለንተናዊ በሆነ መልኩ ድጋፋቸውን ሰጥተዋል፡፡ በተለይም በቃሊቲና አካባቢው የሚኖሩ የክርስትና እምነት ተከታዮች ሚናቸው የጎላ ነበር ማለት ይቻላል፡፡ ጥቂት የማይባሉ ሙስሊሞች ወደየቤታቸው የተመለሱትም ከክርስቲያን ወገኖቻቸው ባገኙት ነጻ ትራንስፖርት (ሊፍት) ነው፡፡ ይህ አጋርነትና ትብብር ወሳኝ በሆኑ አገራዊና ብሄራዊ አጀንዳዎች ላይ ተጠናቅሮ እንደሚቀጥል ተስፋ እናደርጋለን፡፡

የዛሬው ትዕይንተ ዚያራችን ወህኒ ቤት የሚገኙ መሪዎቻችንንና ውድ ወንድሞቻችንን ልእልና አጉልቶ እና ጎዳናዎችን አጥለቅልቆ በሰላማዊ ትግላችን ጉዞ ላይ ሌላ አዲስ ታሪክ አክሎበታል፡፡ ትግላችንም ቀሪውን ትውልድ አስተማሪ ሆኖ እየዘለቀ ነው፡፡ ለሁከትና ግርግር በተመቹ ቦታዎችና በተጋበዝንባቸው አጋጣሚዎች ሁሉ ሰላምን መምረጣችን አስተውሎት ላልተሳናቸው ሁሉ በውስጡ ጥልቅ ትምህርት አለው፡፡

ድል ለኢትዮጵያ ሙስሊም!
አላሁ አክበር!