Thursday, August 30, 2012

እናቴ አወሊያ


Abu Humeyra
እናቴ አወሊያ

የእናት መከራ ማለቂያ የለው እንዲሉ ብዙ ልጆችን የወለደችና የምትወድደው ባሏ የሞተባት አንዲት እናት ነበረች፡፡ይህች እናት ልጆችን እንደ እናትም እንዳበትም ሆና ለማሳደግ ቀን በፀሀይ ሌሊት በቁር ላይ ታች ትባዝን ነበር፡፡ግና የገንዘብ እንጂ የፍቅር ደሀ አልነበረችምና የማያልቀው የናትነት ፍቅሯ ለጨለማው ቤታቸው ብርሀን ነበር፡፡ሲገኝ በልተው ሲጠፋም ተጫውተው ህይወትን ያጣጥሟት ነበር፡፡ቤታቸው የፍቅር ፡የደስታ ና የመከባበር ባንዲራ ሁሌም እንደተውለበለበ ነበር፡፡ ሰው ሁሉ ስለዛ ቤት ፍቅር ያወራ ጀመር፡፡ታዲያ ለሷ አሳቢ ነን ያሉ ቤተ ዘመዶቿ ምንም ሳይራሩ ያለ ፍላጎቷ ለአንድ ክፉ ባል ዳሯት፡፡ ይህ ባል ግዴለሽ፣ ገንዘብ ወዳድ፣ ጠጥቶ ከመስከር፣ በልቶ ከመጥገብ፣ በስተቀር ሌላ ሞያ የሌለው ነው፡፡ ሲወጣ ሲገባ ይደበድባታል፡፡ እንጨት ሽጣ፣ ኩበት ለቅማ፣ እንጀራ ጋግራ፣ ያጠራቀመቻትን ገንዘብ ነጥቆ ይወስድባታል፡፡ እንደፈለገም ይረጨዋል፡፡ ታዲያ ይህች እናት በእንቅርት ላይ ጆሮ ደግፍ እንዲሉ በመከራዋ ላይ መከራ ተደራረበባት፡፡ታዲያ ከዚህ መከራ ሸሸት የት ትሂድ? የአካባቢው ሕግ፣ ባህሉ እና ልማዱ፣ በሙሉ የእርሷን ሮሮ እና ልመና የሚሰማ እንጂ የሚረዳ ፡የሚያይ እንጂ የሚመለከት አልሆነም፡፡ ዘመዴ ያለቻቸውም እዚህ እሳት ውስጥ ከተዋት ጀርባቸውን ሠጥጠዋታል፡፡ሁሉም እርሱን እንደ ሕጋዊ ባልዋ ነውና የሚቆጥሩት ከርሷ ይልቅ እሱ ነው የሚሰሙት፡፡ ታዲያ የት ሂዳ መከራዋን ትናገር ? የትስ ሂዳ ከችግሩ ትገላገል?
ይህ ክፉ ባልዋ እርሷን ብቻ ሳይሆን ልጆቿንም ያሰቃያቸው ጀመር፡፡ እነርሱም በዚያ ቤት ውስጥ መከራውን እና ስቃዩን፣ ረሃቡን እና ጭቅጭቁን እየሰሙ መኖር መረራቸው፡፡ የእንጀራ አባትየው የስካር በትር በማይችል ትከሻቸው ላይ ያርፍ ጀመር፡፡ በቤቱ ይውለበለብ የነበረው የሰላም የፍቅር ባንዲራ ወረደ፡፡ ምንጊዜም የሚሰማው ክፉ እና ልብ የሚያደማ ነገር ሆነ፡፡ ሰው ሁሉ ስለዚያ ቤት ረብሻ ያወራል፡፡ ልጆቹ በዚህ ክፉኛ ተጎዱ ፡፡በመንገድ ላይ ሰው ሲያገኛቸው ስለ ቤታቸው ይጠይቃቸዋል፡፡ እነርሱም በሃፍረት ይሸማቀቃሉ፡፡ ስለዚህም እናታቸውን ጥለው ወደ ሌላ ቦታ መሄድና ስለዚያ ቤት ከማያስቡበት እና ከማይሰሙበት ቦታ ለመሄድ ፈለጉ፡፡ የሚችሉትን ያህል እየሠሩ፣ ለራሳቸው የሚበቃቸውን እየኖሩ፣ መከራውን መገላገል እና እፎይ ብለው መኖር አሰኛቸው፡፡

የሙስሊሙ የመብት ትግል እና የአሜሪካ መንግሥት ‹‹የሃይማኖት ነፃነት ሪፖርት››


Nasrudin Ousman
የሙስሊሙ የመብት ትግል እና የአሜሪካ መንግሥት ‹‹የሃይማኖት ነፃነት ሪፖርት››

• በ‹‹አራምባና ቆቦ›› style የተጻፈ የሁለት ሪፖርቶች ንፅፅራዊ ምልከታ ወይም ትዝብት

የአሜሪካ መንግሥት በየዓመቱ የሃይማኖት ነፃነት ሪፖርት ማውጣቱ የተለመደ ነው፡፡ በዚሁም መንፈስ የ2011/12 ሪፖርት በቅርቡ ይፋ ሆኗል፡፡ በኢትዮጵያ በሃይማኖት ጉዳዮች ረገድ ይህ ዓመት ከቀደሙት ዓመታት በእጅጉ የሚለይባቸው ገጽታዎች እንዳሉት ይታወቃል፡፡ በኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት እና በፌደራል ጉዳዮች ሚኒስቴር ትብብር በሐምሌ ወር 2003 በይፋ የተጀመረውን የአህባሽ ስልጠና ተከትሎ የኢትዮጵያ ሙስሊሞች ላለፉት ዘጠኝ ወራት የመብት ጥያቄዎችን በማንሳት እያካሄዱ ያሉት እንቅስቃሴ ከዓመቱ የሃገራችን የሃይማኖታዊ መብት ጥያቄዎች አኳያ በዐብይነት ይጠቀሳል፡፡ በዚህም ምክንያት የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤት ዘንድሮ የሚያወጣውን የሃይማኖት ነፃነት ሪፖርት በጉጉት ጠብቄው ነበር፡፡ ለነገሩ ጉጉቴ ‹‹እንደው ምን እንደሚጽፉ አይቼ!›› ከሚል ያለፈ አልነበረም፡፡ የዚህን ምክንያት ወደኋላ እመለስበታለሁ፡፡ እነሆ የጻፉትን ሪፖርት አየሁ፡፡ አይቼ አዘንኩ፡፡ ሐዘኔን ለሙስሊም ወገኖቼ አካፍል ዘንድም ከሪፖርቱ እያጣቀስኩ ይህንን ጻፍሁ፡፡ …

ሪፖርቱ በገፅ 5 ላይ እንዲህ ይላል:-

“…There was tension between the traditional Sufi Muslim majority and Muslims affiliated with the so-called “Wahhabist” strain of Islam. The EIASC continued to express concern over the increasing influence of some allegedly Saudi-funded “Wahhabist” groups within the Muslim community, which the EIASC blamed for exacerbating tensions between Christians and Muslims.”

ትርጉም:- ‹‹በብዙኃኑ ነባር ሱፊ ሙስሊም እና ‹‹ወሃቢያ›› በሚሰኘው የኢስላም ወገን መካከል ውጥረት ሰፍኖ ነበረ፡፡ የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት በሳዑዲ የሚረዱ የወሐቢያ ቡድኖች በሙስሊሙ ማኅበረሰብ ውስጥ እያሳደሩ ያለው ተጽዕኖ እንደሚያሳስበው መግለፁን ቀጥሏል፡፡ ጠቅላይ ጉባዔው ይህንኑ ወገን በሙስሊሞች እና በክርስቲያኖች መካከል ውጥረትን ያባብሳል በሚል ወቅሶታል፡፡››

የህዝብ አለመረጋጋት ለአገር ዕድገት እንቅፋት ነው፡፡

የህዝብ አለመረጋጋት ለአገር ዕድገት እንቅፋት ነው፡፡
የፌደራል ጉዳዮች ሚኒስቴር አሰልጣኞችን ከሊባኖስ አምጥቶና በይፋ በግዮን ሆቴል አሳውቆ ሙስሊሙን በአህባሽ የማጥመቅ ዘመቻ ከጀመረ አንድ ዐመት አለፈው፡፡ ሙስሊሙ ህብረተሰብም መጤውን አስተሳሰብ አልቀበልም፤ በግድ ሊጫንብኝም ሆነ ተቋማቶቼን ሊነጥቀኝ አይገባም ብሎ እምነቱን የማስጠበቅ ትግል ከጀመረም እንዲሁ ዐመት ሊደፍን ነው፡፡ በዚህ ሂደት ውስጥ በመንግስት በኩል ለልማት ቢውል ኖሮ በኢኮኖሚ አቅሟ ከመጨረሻዎቹ ተርታ ለምትመደበው አገራችን ተጨባጭ ለውጥ ሊያመጣ የሚችል የነበረ በመቶ ሚሊዮኖች የሚቆጠር ገንዘብ፣ በርካታ ረጃጅም ስብሰባዎች፣ ስልጠናዎች፣ የደህንነትና ፖሊስ ጉልበቶች ባክነዋል፡፡ በሙስሊሙ በኩልም ለስራና ልማት ቢውል ለአገራችን ዕድገት አስተዋጽኦ ሊያመጣ የሚችል የነበረ ቀላል የማይባል ጊዜና ጉልበት መስዋዕት ተደርጓል፡፡ አገራችን ከምንም ነገር በላይ ስለዕድገቷ የሚጨነቅላት ሃይል በምትፈልግበት በአሁኑ ወቅት እንደምን ሆኖ ይሆን ገንዘብና አቅም ሁሉ ወደ ሌላ አቅጣጫ እየፈሰሰ ያለው? ከማናችንም በላይ የአገራችን ዕድገት እንዲያሳስበው የሚጠበቀው መንግስታችን መቼም ይህ ጉዳይ አላሳሰበውም ለማለት ይቸግረናል፡፡ በርግጥ የዕድገት ፀር የሆነና ልማትን የሚያደናቅፍ አካል ካለ የዚህ ዐይነቱን አካል ቅድሚያ ሰጥቶ ማስወገድ እንደሚስፈልግ ሁላችንንም ያስማማናል፡፡ መንግስት ስለ ልማት እያሰበ በሌላ በኩል በአንዳንድ አገራት የምናየው ዐይነት ሰላምን የሚያናጉ የሽብር ተግባራት እየተፈጸሙ ቢሆን ኖሮ ፤ የተለያዩ ሃማኖቶችን አቅፋ በያዘችው አገራችን ያለውን ሁሉ አቀፍ ዲሞክራሲያዊ ስርዐት በመናድ ሃይማኖታዊ መንግስት ህብረተሰቡ ላይ በጉልበት ለመጫን የሚታገል ሃይል ቢኖር ኖሮ አሁንም ቅድሚያ እነዚህን አካላት መዋጋት እንደሚያስፈልግ እናምናለን፡፡

Wednesday, August 29, 2012

Radio Bilal August 29, 2012 አዲስ አበባ ሬዲዮ ቢላል ነሐሴ 23/2004


Radio Bilal August 29, 2012  አዲስ አበባ ሬዲዮ ቢላል ነሐሴ 23/2004

  • በደሴ አረብ ገንዳ መስጅድ የታሰሩ ምዕመናን ለፍርድ እንዳልቀረቡ ተገለጸ
  • ሼህ መሐመድ ሁሴን አልአሙዲን ባለፈው ቅዳሜ በቤተ መንግስት ተገኝተው ሐዘናቸውን እንደገለፁ ተነገረ፡፡
  • ተጠባባቂ ጠ/ሚ ለሁለቱ ሱዳኖች የሰላም ድርድር ድጋፍ እንዲያደርጉ ተጠየቀ
  • ግብፅ ለጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ የቀብር ስነ-ስርዓት ልዑክ እንደምትልክ ገለጸች

Tuesday, August 28, 2012

Radio Bilal Aug 28, 2012 አዲስ አበባ ሬዲዮ ቢላል ነሐሴ 22/2004


Radio Bilal Aug 28, 2012 አዲስ አበባ ሬዲዮ ቢላል ነሐሴ 22/2004

  • ባሳለፍነው ሳምንት በበደሌ ከተማ የተያዙት ሶስት ሰዎች በዋስ መለቀቃቸው ተሰማ
  • በሚዛን ተፈሪ ካለ መጅሊስ ፈቃድ ቁርዓን አስቀርታችኋል በሚል ታስረው የነበሩ ግለሰቦች ተፈቱ
  • ኢትዮጵያና ደቡብ ሱዳን በጋራ  ድንበር ላይ ወንጀሎችን ለመከላለከል ስምምነት ላይ ደረሱ
  • የፍትሕ ዋና አዘጋጅ ክስ ተቋረጠ

Monday, August 27, 2012

ድልን የምንፈልጋት በኛ ጥንካሬ ውስጥ እንጂ በጠላቶቻችን ድክመት ውስጥ አይደለም

ድልን የምንፈልጋት በኛ ጥንካሬ ውስጥ እንጂ በጠላቶቻችን ድክመት ውስጥ አይደለም
አላህ (ሱ.ወ) ይህችን አለም የፈጠረው የሰውን ልጅ ለመፈተን መሆኑን እናውቃለን፡፡ አንዳንዴ መልካም ነገሮችን በመዋል ሲፈትነን ሌላ ግዜ ደግሞ በችግርና በመከራ ይፈትነናል፡፡ ትክክለኛ እምነትና ፅናት ላላቸው ግን ለእያንዳንዷ ችግር መውጫ ቀዳዳ ተበጅቶላታል፡፡ እኛም ኢትዮጵያውያን ሙስሊሞች የእምንት ጥንካሬያችን እና ፅናታችን የሚፈተንበት ግዜያዊ ፈተና ከወደቀብን አመት ሊሞላን ነው፡፡ ግዜው አመት መሙላቱ በአንድ በኩል የፈተናችን ግዜ በአጭር አለመቀጨቱን ሲያመላክተን በሌላ በኩል ደግሞ በተደቀነብን ፈተና ሳንሸነፍ ለአመት መፅናታችንን ያሳያል፡፡ ካሉት ነባራዊ ኩነቶች አንፃር የሁለተኛው መላምት ይበልጥ ለእውነት የቀረበ ነው፡፡

Radio Bilal August 27, 2012 ሬዲዮ ቢላል ነሐሴ 21/2004


Radio Bilal August 27, 2012 ሬዲዮ ቢላል ነሐሴ 21/2004

  • ዛሬ ይጀመራል የተባለው የመጅሊስ ምርጫ መራዘሙ ተገለጸ
  • በማልታ የሚገኙ ኢትዮጵያዊያን ሙስሊሞች ቢላል ኮሚኒኬሽንና ዓለም  አቀፍ የኢትዮጵያዊያን ሙስሊሞች ም/ቤትን ለመደገፍ ቃል መግባታቸው ተገለጸ
  • አወሊያ ኮሌጅ ግልፅ ባልሆነ ምክኒያት ምዝገባ እንዳልተጀመረ ተጠቆመ
  • በደሴ በተከሰት ግርግር ላይ የታሰሩ ምዕመናን ነገ ለፍርድ እንደሚቀርቡ ተገለፀ

Radio Bilal August 26, 2012 አዲስ አበባ ሬዲዮ ቢላል ነሐሴ 20/2004


 
  • የአየር ጤና አንሷር መስጅድ ኮሚቴ በ10 ሚሊዮን ብር ወጪ ያስገነባው ሕንፃ ለአገልግሎት ተዘጋጀ
  • በሚዛን ተፈሪ ስምንት ሙስሊም ግለሰቦች መታሰራቸው ተጠቆመ
  • በሻሸመኔ ወረዳ ሙስሊሙ ህብረተሰብ በመጅሊስ ምርጫ እንዲሳተፍ እየተገደደ እንደሆነ ነዋሪዎች ጠቆሙ
  • ፕሬዝደንት ባራክ ኦባማ ተጠባባቂ ሚኒስትሩ ለሰብዓዊ መብቶች መከበር ትኩረት እንዲሰጡ ጠየቁ

Saturday, August 25, 2012

Radio Bilal August 25, 2012 ሬዲዮ ቢላል ነሐሴ 19/2004


Radio Bilal August 25, 2012 ሬዲዮ ቢላል ነሐሴ 19/2004

  • በኢድ ሰላት ታስረው የተፈቱት ምዕመናን ፍረድ ቤት እንደሚቀርቡ ተጠቆመ
  • ነሀሴ 21 ሊካሄድ የነበረው የመጅሊስ ምርጫ መራዘሙ እየተነገረ ነው
  • ታዋቂ ሰዎችና አምባሳደሮች በጠ/ሚ መሞት ሀዘናቸውን እየገለፁ ይገኛሉ
  • የፍትህ ጋዜጣ ዋና አዘጋጅ የዋስ መብት በመከልከል መታሰሩ ተጠቆመ

Friday, August 24, 2012

CNN


ኮሚቴዎቻችን ሳይፈቱ ገለልተኛ የምርጫ አስፈፃሚ ሳይመረጥ በምርጫዉ አንሳተፍም




  • በሀረር ከተማ በኢማን መስጂድ በሺዎች የሚቆጠሩ ሙስሊሞች ከጁምአ ሰላት ቡሀላ ኮሚቴዎቻችን ሳይፈቱ ገለልተኛ የምርጫ አስፈፃሚ ሳይመረጥ በምርጫዉ አንሳተፍም በማለት በከፍተኛ ሁኔታ ተቃዉሟቸዉን ማሰማታቸዉን ምንጮቻችን አስታወቁ:: በተመሳሳይ ሁኔታም በአማራ ክልል በኦሮሚያ ዞን በዳዌ ወረዳ ከጁምአ ሰላት ቡሀላ ህዝበ ሙስሊሙ ጥያቄዎቻችን ይመለሱ በማለት ከፍተኛ ተቃዉሞ ማሰማታቸዉን ምንጮቻችን አስታወቁ:: አላሁ አክበር!!!
     

    ድምፃችን ይሰማ

    በወላይታ ዞን በቦዲቲ ከተማ ከጁምአ ሰላት ቡሀላ የዞኑ መጅሊስ ተብየዎች ለህዝበ ሙስሊሙ የምርጫ ቅስቀሳ ለማድረግ የሞከሩ ሲሆን በአዲስ አበባ ከተማ የሚኖሩ ሙስሊሞች በአጠቃላይ ለምርጫዉ ተመዝግበዎል እናንተም አሁን በፍጥነት ተመዝገቡ አለበለዚያ ግን አልመዘገብም ያለ ይታሰራል ይሰቃያልም በማለትለ ለማስፈራራት መሞከራቸዉን ምንጮቻችን አስታወቁ:: ህዝበ ሙስሊሙም ማስፈራሪያዉና ዛቻዉ ሳይበግራቸዉ በከፍተኛ ቁጣ ኮሚቴዎቻችን ሳይፈቱ ምርጫ የሚባል ነገር አናዉቅም!!! ኮሚቴዎቻችን ይፈቱ!! በማለት በከፍተኛ ተክቢራ ተቃዉሟቸዉን ማሰማታቸዉን የአካባቢዉ ምንጮች አስታዉቀዎል:: አላሁ አክበር!!!


  • በወለጋ መጫራ ከተማ ነሐሴ 16 መንግስት ባካሄደዉ የመጅሊስ አመራሮች ምርጫ አስፈፃሚዎች ምርጫ መንግስት በራሱ የመረጣቸዉ ግለሰቦች በመሆናቸዉ እና የተመረጡት ሰዎችም በጥንቆላ ስራ ላይ የተሰማሩ ሰዎች በመሆናቸዉ የአካባቢዉን ሙስሊሞች ወክለዉ ምርጫ አስፈፃሚ መሆን የለባቸዉም በማለት ህዝቡ በራሱ ምርጫ የፈለግነዉን ምርጫ አስፈፃሚ አድርገን መምረጥ አለብን በማለት መንግስት የመረጣቸዉን ግለሰቦች ህዝቡ አልቀበልም በማለቱ እስካሁን በደረሰን መረጃ መሰረት 10 ሰዎች መታሰራቸዉን ምንጮቻችን ዘግበዎል:: በተመሳሳይም በበደሌ ከተማ ኮሚቴዎቻችን ሳይፈቱ ምርጫዉን አንሳተፍም ያሉ 15 ሙስሊሞች መታሰራቸዉ ተሰምቷል:: እንዲሁም በአጋሮ ከተማ የመጅሊስ ምርጫን እንዲያስፈፅሙ መንግስት የመረጣቸዉን ግለሰቦች የከተማዎ ሙስሊሞች አንቀበልም በማለታቸዉና ኮሚቴዎቻችን ሳይፈቱ ምርጫዉን አንካፈልም በማለታቸዉ የመንግስት አካላት በየቤቱ እየዞሩ በከፍተኛ ሁኔታ ማህበረሰቡን እያስፈራሩ እንደሚገኙም የአካባቢዉ ምንጮች አስታዉቀዎል::


  • በጎንደር ከተማ የመጅሊስ አመራሮችን ምርጫ ለማካሄድ መንገስት ባዘጋጀዉ 15 የምርጫ ጣቢያ የምርጫ አስፈፃሚና የምርጫ ታዛቢዎች መመረጣቸዉ ተሰማ:: በሚያስገርም ሁኔታም የምርጫ አስፈፃሚ ተብለዉ ከተመረጡት መካከል በግንባር ቀደምትነት የጎንደር ከተማ የአህባሾቹ ኡለማ ምክር ቤት ሊቀመንበር የሆኑት ሙስጦፉ አሚኑ እና የሳቸዉ ዎና ፀሀፊ የሆነ መሀመድ ሳልህ ይገኙበታል:: ሙስጠፉ አሚኖ የሚባለዉ ግለሰብ በጎንደር የአህባሽ አስተሳሰብ ፊት አዉራሪ ሲሆን በየመስጂዱ በመዞር የኢትዮጲያ ታዎቂ ዳኢ የሆኑትን ኡስታዝ ያሲን ኑሩን, በድሩ ሁሴንን, ሀሰን ታጁን እንዲሁም አለም አቀፍን ዳኢ ዶ/ር ዛኪር ናይክን ካፊሮች ናቸዉ በማለት በአደባባይ የሚያስተምር ግለሰብ መሆኑን የጎንደር ምንጮቻችን ገልፀዎል::በአሁኑም ወቅት በየቀበሌዉ የነ ሼህ ሙስጠፉን ቡድን (አህባሽን) ያልመረጠ አሸባሪ, ወሀቢይ, ካፊር ፀረ ሰላም ነዉ ወ.ዘ.ተ....... እየተባለ በከፍተኛ ደረጃ ቅስቀሳ እየተደረገ እንደሚገኝ ምንጮቻችን ገልፀዎል:: የጎንደር ወጣት ሙስሊሞች ግን ኮሚቴዎቻችን ከእስር ሳይፈቱ ምርጫ የማይታሰብ ነዉ በማለት በአቖማቸዉ ፀንተዉ እንደሚገኙ ነዉ የጎንደር ምንጮቻችን ያስታወቁት!!!!


 ድምፃችን ይሰማ
በስልጤ ዞን አሁንም ማዋከቡና ማሰሩ ቀጥሏል፡፡ በትላንትናው እለት አቶ ሰላሃዲን የሚባል ወራቤ መናኻርያ የሚሰራ ልጅ ከዚህ በፊት የውሸቱን ድጋፍ ሰልፍ እንዳይወጣ ቀስቅሰሃል ተብሎ ታስሮ ነበር፡፡ አሁንም በጠቅላይ ሚንስተሩ ሞት ተደስተሃል ብለው አሰሩት ፡፡ ወላሂ በጣም ይገርማል መብቱ መሰለኝ እኮ ደስ ቢለው የራሱን አስተሳሰብ በነጻነት ማራመድ ይችላል ተብሎ ህገ መንግስቱ ላይ እኮ ተፏል፡፡ ስልጤ ዞን ማለት ሆድ አምላኩ ሙጅሪም አመራር የተሰበሰበበት ነወ፡፡ ከዚህ ጋር በተያየዘ ከዚህ በፊት እንደነገርኳችሁ ከሳንኩራ ወረዳ 14 ልጆች አህበሽን በመቃወማቸው መታሰራቸው ይታወሳል፡፡ ከ14 ልጆች ውስጥ 8 መፈታታቸውና 6 ቱ እስከ አሁን እንዳልተፈቱ ተነግሮዋል፡፡ በመቀጠልም ምርጫውን አስመልክቶ ትላንትና የወራቤ ከተማ ከንቲባ የሆኑት የአቶ ሙርሰል አማን አባት፣ የእህቱ ባል የወራቤ ከተማ ስፖርት ጽ/ቤት የሆኑት አቶ ከድር ሼ /ሙዘይን አባት የሆኑት ሼ/ሙዘይን ሼ/ሰኢድ ከፍተኛ የአህባሽ አቀንቃኝና አመራር እንዲሁም አቶ ከማል አህመድ የሜላት ካፌ ባለቤት የሆኑት ለመጅሊስ ምርጫ መመረጣቸውን ነግሬያችሁ ነበር፡፡ ይህ በእንዲህ እንዳለ አስመራጭ ኮሚቴውን በተመለከተ ትላንትና በወራቤ የተመረጡ ሰዎች ስብሰባ የተጠሩና በፖሊስ ታጅቦ እንዲገቡ የተደረገ ሲሆን ልክ ድርጅት ላይ ምርጫ ሲደረግ ሰዎች ተዘጋጅተው እከሌን ምረጥ ተብሎ ይዘጋጅና ሰው እጅ ሲያወጣ ለማን ለማን እንደሚሰጥ ማንን እንደሚመርጡ ተነግሮዋቸው ልክ ድርጅት ላይ እንደሚሰሩት የመጅሊስ አስመራጭ ኮሚቴ ማስመረጣቸው ተገልጾል፡፡ ከነዚህም ውስጥ በአብዛኛው የጎጥ አመራሮች/የፖለቲካ አቀንቃኞች/ ተካተዋል፡፡ በጣም የሚገርመው ሃጂ ሻፊ የአቡበከር መስጂድ ኢማም የሆኑት በሰደቃ ፕሮግራሙ ላይ ምርጫ መስጂድ ካልሆነ አንመርጥም ሲሉ የነበሩ ሲሆን አሁን ግን የአቋም መዋዠቅ ታይቶባቸው ምርጫው በቀበሌ መሆኑን ደግፈው እየሰሩ ይገኛሉ፡፡ እኛ የወራቤ ነዋሪዎችም እንደዚህ አይነት እኩይ ተግባራትን የሚሰሩትን ሁሉ አጋልጦ ማውጣት አለበት፡፡ በተጨማሪም በተለያዩ ቦታዎች ላይ የኢድ ሰላት በከፍተኛ ተቃውሞ መደረጉ የሚታወስ ሲሆን በወራቤ ከተማ ግን እነ ሃጂ አብዱልሃዲ ቡርሃን የሪያድ ሆቴል ባለቤት ህዝቡን በማሰመንና በመለመን ምንመ ተቃውሞ እንዳይደረግ ከፍተና አስተዋጽኦ አድርጓል፡፡ ሃጂ አ/ሃዲ ከፍተኛ አክብሮትና ተሰሚነት ስላላቸው ነው፡፡ በአሁኑ ሰአት ውስጥ ለውስጥ ቀጣይ ስትራቴጂዎችን እየሰራን እንደሆነ እና ሁላችንም የስልጤ ዞን ሆዳም አመራሮች የሚሰሩትን ስራ ተከታትለን እንድናጋልጥና በዚህ በቤተ ዘመድ ጉባኤ ምርጫ እንዳንሳተፍ መልእክቴን አስተላልፋለው፡፡ በዚህ አጋጣሚ ተጨማሪ መረጃዎች ያሏችሁ ሰዎች መረጃ ለሙስሊሙ በመስጠት ለጥቅም ዲናቸውን የሸጡ አመራሮችን እናጋልጥ እላለሁ

Thursday, August 23, 2012

አስቸኳይ ማሳሰቢያ
(ነሐሴ 17 2004)

አገራችን ኢትዮጵያ በአሁኑ ሰዓት በከባድ የሐዘን ድባብ ውስጥ ትገኛለች፡፡ በመላ አገሪቱም የሀዘን ቀን ታውጆ ባንዲራዎች ዝቅ ብለው እየተውለበለቡ ዜጎችም የሀዘን ስሜታቸውን በተለያዩ አጋጣሚዎች እየገለጡ ይገኛሉ፡፡ የዓለም አገራትም ከአገራችን አልፎ አሕጉራዊ የጎላ ሚና በነበራቸው ጠቅላይ ሚንስትር ሞት የተሰማቸውን ሀዘን እየገለጡ ኢትዮጵያችንም ይህንን ሁኔታ እያስተናገደች ትገኛለች፡፡

ያለፉትን ከ290 ቀናት በላይ በምን መልኩ እንዳሳለፍናቸው እንቃኛቸው፡፡

ይኸው በታዳጊና ወጣት የአወሊያ ተማሪ ወንድሞቻችንና እህቶቻችን የተጀመረው ሃይማኖታዊና ህገመንግስታዊ መብቶቻችንን የማስከበር ትግላችን አንድ ዐመት ሊደፍን ከሰባ የማይበልጡ ቀናቶች ብቻ ቀርተውታል፡፡ የትግላችን ዐይነተኛ ባህሪ ሰላማዊነት ነው፡፡ ሰላማዊነት ሲባል ህግ አክባሪነትን፣ የሌሎችን ዜጉች ፀጥታና ደህንነትን መጠበቅን እንዲሁም በጥቅሉ ህግና ስርዐት አለመደፍረሱን ማረጋገጥ ጭምር ነው፡፡ እስኪ ከዚህ አንጻር ያለፉትን ከ290 በላይ ቀናት በምን መልኩ እንዳሳለፍናቸው እንቃኛቸው፡፡ ገና ከጅምሩ በጀግኖቹና ከዕድሜያቸው በሚልቅ ርዕይ በአወሊያ እንድንሰባሰብ ግብዣ ባቀረቡልን የአወሊያ ተማሪዎች ጥሪ ከተሰባሰብንና የሃይማኖታችን
መደፈር፣ የእምነታችን በእኩያን መነካት አስቆጥቶን መሪ ኮሚቴዎቻችንን ከመረጥንበት ጊዜ አንስቶ ሁነኛ መርኃችን ሰላም፣ ህግና ስርዐት ማስጠበቅ ነበር፡፡ ኮሚቴዎቻችንም በህዝብ ከተወከሉበት ቀን አንስቶ ሲያንፀባርቁት የነበረውም መርህ ይህንኑ ነው፡፡ ኮሚቴዎቻችን በህዝብ ሲመረጡ የተሰጣቸው ውክልና በኢትዩጲያ ሙስሊም ህብረተሰብ ስምና ፊርማ እንዲረጋገጥና ህዝቡም ውክልናውን ህግና ስርዐቱ በሚጠይቀው መልኩ እንዲያጸድቅላቸው ያደረጉት ጥረት ገና ከጅምሩ ለህግ መከበር ያላቸውን ቁርጠኝነት አመላካች ነበር፡፡

Wednesday, August 22, 2012

Radio Bilal News August 22, 2012


በቡራዩ ከተማ የመጅሊስ ምርጫ ሊካሄድ እንደሆነ ነዋሪዎች አመለከቱ

በስልጤ ዞን የመጅሊስ ምርጫ ቅስቀሳ መጀመሩ ተገለፀ

የታሰሩ ሙስሊሞች እንዲፈቱ ሂውማን ራይት ዎች እና ሲፒጄ ጠየቁ

በትላንትናው ዕለት በወሊሶ ከተማ የመጅሊስ ምርጫ አስመልክቶ ስብሰባ ተካሄደ

የወለኔ ህዝቦች ዲሞክራሲያዊ ፓርቲ አባላት ታሰሩ

ከ2.5 ሚሊየን ህዝብ በላይ ምእመናን በተገኙበት የተቃውሞ ሂደት ያለምንም ልዩነት ህዝቡ አንድ አይነት ተቃውሞ ሲያሰማ ነበር፡፡

by Meranu Habibti
ለጀርመን ሬድዮ ጣቢያ ዘጋቢ ጌታቸው ተድላ” እውነቱ ይህ ነው”
በቅድሚያ ለዚህ ፅሁፍ አንባቢዎች በሙሉ ልባዊ የሆነ ሰላምዬ ባላችሁበት ይድረሳችሁ፡፡ብዘገይም ለሙስሊም ወንድሞችና እህቶች እንኳን ለኢደልፊጥር በዐል በሰላም አደረሳችሁ እላለሁ፡፡ከኢድ ሰላት መልስ እንደሌሎች ሁሉ እኔም የኢድ ሰላትና ሰላማዊ ተቃውሞው በሰላም እንደተጠናቀቀ ፖስት አድርጌ በኢዱ እለት የነበረውን ድባብና የህዝቡን ስሜት በተመለከተ አጭር ፅሁፍ ለማቅረብ (በተለይ ከሃገር ዉጭ ያሉ ኢትዮፕያውያን ስለጠየቁኝ) እንደምሞክር ቃል ገብቼ የነበረ ቢሆንም በግል ችግር ምክንያት ሁኔታዎች አልተመቻቹልኝም ነበርና ቃል በገባሁት መሰረት ለማቅረብ ባለመቻሌ ይቅርታ እንድታደርጉልኝ እጠይቃለሁ፡፡

Tuesday, August 21, 2012

Another repression of Muslims and Islam – This time in Ethiopia


eth









Cii News, – August 16, 2012
The Ethiopian government has angered millions of Muslims in the country by arresting at least 17 prominent Muslim leaders following weeks of peaceful protests against attempts to impose a foreign Islamic ideology upon them. .
The brutal crackdown and mass arrests, since July 13, came after hundreds of thousands of Muslims joined huge demonstrations took to the streets calling for the government to stop interfering in their religious practices .

ኮሚቴው ሳይፈታ በምርጫው አንሳተፍም!!

ኮሚቴው ሳይፈታ በምርጫው አንሳተፍም!!
የህዝብ ውክልና የሌለውና በማን አለብኝነት ያሻውን ሲገነባና ሲንድ የኖረው ህገወጡ መጅሊስ ያስቀመጠው የምርጫ የግዜ ሰሌዳ እነሆ በጣት የሚቆጠሩ ቀናት ይቀሩታል፡፡ መላው የሃገራችን ህዝብም በድምፁ መታፈንና በጥያቄው ምላሽ ማጣት ከፍተኛ ቅሬታ ውስጥ ገብቷል፡፡ የመንግስት ባለስልጣናት ምርጫውን አስመልክቶ የመወሰን ስልጣን የህዝቡና የህዝቡ ብቻ ነው ብለው ቢያሳውቁም የመጅሊስ አመራሮች ግን ማንስ ምን አገባው በሚል አምባገነንነት ምርጫውን በቀበሌና እኔ ባሰብኩት ሂደት ከማድረግ ወደኋላ የሚለኝ አንዳችም ሃይል የለም እያለ ይገኛል፡፡ ድምፁን ከማሰማትና ወደፈጣሪው ስሞታውን ከማቅረብ ውጭ አማራጭ የሌለው ህዝበ ሙስሊምም እጃችሁን ጠምዝዘን ከሂደቱ ማስወጣት ባንችልም በሂደቱ ላይ የራሳችንን አቋም ከማንፀባረቅ የሚያግደን የለም ሲል ሚሊዮኖች ሆኖ በዒድ አደባባዩ ድምፁን አሰምቷል፡፡ ከፊታችን ያለውን ምርጫ መሳተፍና አለመሳተፍ ከበርካታ ነጥቦች አንፃር የሚታይ ቢሆንም የኮሚቴዎቻችን ጉዳይ ግን ልዩ ትኩረት የሚሻው መሆኑ ሁላችንንም ያስማማናል፡፡ ምርጫውን እንደ አንድ አጀንዳ ብቻውን ነጥለን ከተመለከትነው በቀጣዩ የመጅሊስ መዋቅር ውስጥ በህዝብ ድምፅ የተመረጡ ወኪሎች ማግኘት ከመቻልና ምርጫን አንሳተፍም ማለት ያለውን ኪሳራ እንደ ትልቅ ጉዳት አድርገን ልንመለከተው እንችላለን፡፡ ይህ ሁላችንንም የሚያግባባን ጉዳይ ነው፡፡ ነገር ግን ምርጫውም ሆነ ሂደቱ በሚያሳዝን መልኩ የህዝብን ፍላጎት በረገጠና ለማወያየት እድል እንኳን ባልሰጠ አካሄድ እየተተገበረ ሊያሳስበን የሚገባው ወሳኙ ጉዳይ የአጠቃላይ መብታችን ጉዳይና የህዝባችን ስሜት መሆኑ አሳማኝ ሆኖ ተገኝቷል፡፡ በዚህም መሰረት በሌሎች ነጥቦች ዙሪያ በርካታ ትንተናዎች ሊሰጡ ቢችሉም ምርጫው በቀበሌም ይሁን በመስጂድ፡-

Monday, August 20, 2012

قضية وحوار | مسلمو إثيوبيا

ህዝባዊ/ ልማታዊ/ ዲሞክራሲያዊ/ ሆደሰፊው… መንግስታችን ከአርባ ሚሊየን ህዝብ ልብ ተፋቀ !!! ።


ህዝባዊ/ ልማታዊ/ ዲሞክራሲያዊ/ ሆደሰፊው… መንግስታችን ከአርባ ሚሊየን ህዝብ ልብ ተፋቀ !!! ።
የትላንቱ የኢድ ሰላት ታላቅ ህዝባዊ ሰላማዊ ተቃውሞ ከላይ በጠቀስናቸው እራሱን በራሱ በሰየመባቸው የማእረግ ስሞቹ ለሚታወቀው መንግስታችን ከህዝብ ልብ መፋቅ ታላቅ ተጨባጭ መረጃ ነበር። እንደሚታወቀው የኢዱ ቀን ከመድረሱ በቀናት ቀደም ብሎ መንግስት ጉንፋኑን የሚያስነጥስበት በሆነው ቴሌቪዥኑ (ETV) በየእለቱ በሚያቀርባቸው ዜናዎች አራት ወይንም አምስት ግለሰቦችን በማቅረብ ህዝበ ሙስሊሙ በታላቁ የኢድ ሰላት ላይ ምንም አይነት ሰላማዊ ተቃውሞን እንደማያሳይ ሲገልፅ ነበር። እኔም ቤቴ ውስጥ ከአባቴ ጋር ቁጭ ብየ ዜናዎቹን ስከታተል ይህ ነጩን ጥቁር፣ ጥቁሩን ነጭ እያለ የሚዘግብ የቴሌቪዥን ጣብያ ያንን ሁሉ የህዝብ ድምፅ “የጥቂቶች” ሲል ቆይቶ አራት እና አምስት ግለሰቦችን “ህዝበ ሙስሊም” እያለ መጥራቱ በጣሙን ስለደነቀኝ!!!፤ እነዚህ ግለሰቦች ናቸው እንዴ ህዝበ ሙስሊሙ? ብዬ ለአባቴ ብጠይቅ የሰጠኝ ምላሽ ፈገግ አስደርጎኝ ስላለፈ ለናንተ ላካፍላቹ ወደድኩ። ምን አለኝ መሰላቹ “ምናልባት እኛ ወላጆቻችን ስም ሲያወጡልን አህመድ፣ መሀመድ… እንዳሉን ሁሉ ለነዚህ ሰዎችም ወላጆጃቸው ያወጡላቸው ስም “ህዝበ ሙስሊሙ” የሚል ሊሆን ይችላል ስለዚህም ጣብያው ህዝበ ሙስሊሙ ማለቱ የሰዎቹን ስም ለመጥቀስ ሳይሆን አይቀርም!!!፤” ብሎኝ ፈገግ አሰኝቶኛል።

Ethiopian Muslim stick to nonviolence to overcome the regime’s divisive and repressive tactics

 Jawar Mohammed|August 20, 2012


Ethiopian Muslims have been staging weekly protest, every Friday, to demand government respect their religious freedom. Specially they demand the government to stop  the ongoing stop forced imposition is an alien religious doctrine imported from Lebanon, and allow them to freely elect leaders of Mejlis,  their central institution.  Instead of addressing  this simple demands, the regime has attempting to repress, divide and mislabel the protesters. This article looks at how Muslim protesters have been utilizing methods of nonviolent resistance to overcome  the regimes repressive and divisive campaigns.
Why is the regime messing with religion?
As an authoritarian system built on a slim power base and lacking popular legitimacy, the TPLF has been able to prolong its reign through two important tactics that complement its use of brutal force.  First, by dividing the population across all imaginable segments, and second, by destroying, co-opting, or corrupting existing social institutions and obstructing development of new ones. Religious institutions have been one of the primary targets.

Sunday, August 19, 2012

ከፊል የዒድ የተቃውሞ ትዕይንት በጂማ

Aljazeera reports The Huge Eid Protest.

ድምፃችን ይሰማ
በሚሊዮን የሚቆጠር ህዝበ ሙስሊም ታሪክ ሰራ!!!
በመላዉ ኢትዮጲያ የሚገኙ ሙስሊሞች ከኢድ ሰላት ቡሀላ ከፍተኛ ተቃዉሟቸዉን በማሰማት በኢትዮጲያ ታሪክ ዉስጥ የማይረሳ ታሪክ መስራታቸዉ ተገለፀ:: በመላዉ ሀገሪቱ የተካሄዱት ተቃዉሟዎች ፍፁም ተመሳሳይ ይዘት የነበራቸዉና ፍፁም ሰላማዊ ሆነዉ የተካሄዱ ነበሩ:: በተቃዉሞ ሰልፍ ላይ ህዝበ ሙስሊሙ ድምፃችን ይሰማ; ኮሚቴዎቻችን ይፈቱ; በግፍ የታሰሩ ንፁሀን ሙስሊሞች ይፈቱ; ምርጫችን በመስጂዳችን; ኮሚቴዎቻችን ሳይፈቱ ምርጫ የለም; ሀስቡን አላህ ወኒ አመል ወኪል; ህገ መንግስቱ ይከበር, ኢስላም ሰላም ነዉ; እኛ አንድ ነን አንለያይም; አሻዕብ ዩሪድ ኢስቃጠል መጅሊስ; አሸባሪዎች አይደ

ለንም; ጥቂቶች አይደለንም; ጥያቄዎቻችን ይመለሱ; ኢቲቪ ዉሸታም; ኢቲቪ ሌባ; ዉሸት ሰለቸን; ፖሊስ የህዝብ ነዉ; ዉሾቻችሁን እሰሩልን; አፈናና እስራቱ ይቁም; የሚሉ በርካታ መፈክሮች ህዝበ ሙስሊሙ በመላዉ ሀገሪቱ ሲያሰማ እንደነበር ለማወቅ ተችሏል:: ተቃዉሞ ከተካሄደባቸዉ ከተሞች መካከል በጣም በጥቂቱ የሚከተሉት ይጠቀሳሉ:: በአዲስ አበባ ከተማ, በጅማ ከተማ, በአዳማ ከተማ, በድሬዳዎ ከተማ, በደሴ ከተማ, በአማራ ክልል በወሎ ከሚሴ ከተማ,በአማራ ክልል በደጋን ከተማ, በሰበታ ከተማ, በአፉር ክልል በዞን አምስት በዳዌ እና በኢሊወሀ ከተሞች, በአጋሮ ከተማ, በትግራይ ክልል በእደጋሀሙስ ከተማ, በወለጋ ጊንቢ ከተማ, በስልጤ ዞን ሳንኩራ ወረዳ, በሮቤ ማዳወላቡ ከተማ , በወላይታ እና በመጫራ ከተሞች ሰላማዊ ተቃዉሟዎችን ህዝበ ሙስሊሙ ካሰማባቸዉ ከተሞች መካከል በጣም ጥቂቶች ናቸዉ:: በሁሉም ቦታዎች የተካሄዱት ተቃዉሞዎች በሰላም የተጠናቀቁ ሲሆን በአዳማ ከተማ በተካሄደዉ ሰላማዊ ሰልፍ ላይ ግን ፓሊስ የከተማዎን ሙስሊሞች በመደብደብ ለመበተን መሞከሩን ምንጮቻችን ገልፀዎል:: በመላዉ ሀገሪቱ ሰላማዊ ትግሉ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ህዝበ ሙስሊሙ አረጋግጧል!!! አላሁ አክበር!!!
በድምጻችን ይሰማ
በአላህ ሥም እጅግ በጣም አዛኝ እጅግ በጣም ሩህሩህ

ኢትየጵያዊያን ሙስሊሞች አኩሪ ታሪክ ሠሩ
አዲስ አበባ ስታዲየም ልዩ የተቃውሞ ትዕይንት አስተናግዶ ዋለ፡
ሙስሊሙ ሀዝብ ለ9 ወራት ይዞት የዘለቀውና ተገቢ ምላሽ ሳያገኝ ንቀት በተሞላበት ሁኔታ እያስተናገደ የሚገኘውን ሀይማኖታዊ የመብት ጥያቄ አካል የሆነው ተቃውሞ በታሪኩ ልዩ እና ፍፁም ሠላማዊ በሆነ መልኩ ተካሂዷል፡፡ ሰፊውን ህዝብ ያቀፈ መሰረታዊ የመብት ጥያቄ ባግባቡ በማስተናድ ተገቢውን ምላሽ ከመስጠት ይልቅ “ጥቂቶች” በሚል አባዜ ተጠምዶ ለከረመው አካል ትልቅ ትምህርት የሰጠ የተቃውሞ ውሎ ሆኗል፡፡ ገና በማለዳ ወደ ስቴዲየም መጉረፍ የጀመረው ሙስሊም ህዝብ አመጣጡ እንደ
እስከዛሬ ዒድን ብቻ ለመስገድ እየመጣ እንዳልነበረ ከአብዛሃኛው ሙስሊም ገፅታ በቀላሉ ማንበብ ይቻል ነበር፡፡ ትላንት የመግሪብ ሰላት መሰገድን ተከትሎ በየመስጂዱ እና አካባቢው ያለውን የጠነከረ ቁጥጥር በማለፍ የዛሬውን የዒድ የተቃውሞ ውሎ አቅጣጫ የሚያሳዩ ወረቀቶች ሲበተኑ ያመሹ ሲሆን ይህም በስታዲየም ለሚኖረው የተቃውሞ ሂደት መልክ ያበጀ እና ሂደቱ በተፈለገው መንገድ ተጉዞ ውጤታማ ሊሆን እንደሚችል አመላካች ነበር፡፡

More videos of non Violent protest After 2012 Eid Salat in Addis Ababa a...

Nationwide Huge Protest After Eid Salat in Addis Abeba, Dessei, Jimma , ...

Protest after Eid Salat in Adama Ethiopia. , August 19th , 2012

Protest after Eid Salat in Addis Ababa , August 19th , 2012

Friday, August 17, 2012

NZ-based Ethiopians protest over delayed elections ‘torture’

Pacific Scoop
Report – By Jessi Mee
Muslims in Ethiopia are being detained and tortured for speaking against the government’s plan to control the Muslim representatives election, say New Zealand-based protesters.
The Islamic Affairs Supreme Council in Ethiopia is supposed to have a national election every four years.
There has not been one in more than a decade.
More than 60 Muslim protesters marched down Auckland’s Queen Street in a protest last week chanting their support for a peaceful struggle for justice in Ethiopia.
They were protesting for rights – not for their own, but for those of their fellow countrymen who they claim are being persecuted because of their Muslim faith.

ዒድ ሙባረክ

ዒድ ሙባረክ
ተቀበለላሁ ሚና ወሚንኩም ሳሊሀል አዕማል
ውድ ሙስሊሞች እየተፈፀመብን ያለው ግፍ፣ እየደረሰብን ያለው የመብት ረገጣና የህግ ጥሰት እንዲሁም ዲናችንን የሚያራክሱ ተግባራት በዚህ ታላቅ የዒድ በዓላችን በከተማችን የምንገኝ ከ1 ሚሊዮን የምንልቅ ሙስሊሞች አንድ በመሆን በዲናችን እንደማንደራደርና ዘብ እንደምንቆም በተግባር እንድናሳያቸው አስገድዶናል፡፡ በመሆኑም በዚህ ታላቅ የሙስሊሞች ቀን ስግደታችንን ፈፅመን ከፍተኛ የተቃውሞ ድምፅ በሰላማዊ መንገድ ከአጥናፍ እስከ አጥናፍ እናሰማለን!! ህዝብ ነንና ማንም ሊነፍገን የማይችለው ተቃውሞን የማሰማት ሙሉ መብት አለን፡፡ ስለዚህ ጥያቄያችን እንዲመለስ ኮሚቴዎቻችን እና የታሰሩት ሁሉ እንዲፈቱ እንጠይቃለን!! ውድ ሙስሊሞች የተቃውሞው ይዘት ከወትሮው የሚለየው ጥያቄዎቻችን የሚሊዮኖች መሆናቸውንና ወኪሎቻችን የሁላችንም መሆናቸውን ዳግም በአደባባይ ለመመስከር ሲሆን በተዛባ መረጃም ይሁን መረጃን ካለማግኘት የትግላችንን ሂደት ላልተረዱ ሁሉ ሰላማዊነታችንን በተግባር በማሳየት መንግስትም ህዝብንና ሃገርን የሚጠቅም ፍትሃዊ ምላሽ እንዲሰጠን ለመጠየቅ ነው፡፡ የተቃውሞ ሂደቱ ከዚህ እንደሚከተው ብቻ ይሆናል፡

Ethiopia: Standing up with our Muslim citizens

Ethiopia: Standing up with our Muslim citizens
nazret.com
By Yilma Bekele

The TPLF regime is the kind that believes in a proactive stance in their approach to ward off unwanted happenings. They learned that during the war with the Derg. It is said that upon taking over a village their first act was to gather the village heads and kill those that don’t agree with them, humiliate a few to teach the rest a lesson and recruit the weak to use and abuse. That system sharpened and enhanced has served them to stay in power.

እንኳን ለ1433ኛው የዒድ አልፈጥር በዓል በሰላም አደረሰን

እንኳን ለ1433ኛው የዒድ አልፈጥር በዓል በሰላም አደረሰን
እኛ ኢትዮጵያውያን ሙስሊሞች በእድሜያችን ከፆምናቸው ረመዳኖች የዘንድሮው በብዙ መልኩ እንደሚለይ ለማንም የተደበቀ አይደለም፡፡ እርስ በእረስ እንድንባላ ከተደገሰልን ድግስ አምልጠን ለወሩ ክብርና ሞገስ በሚገጥም የአንድነት እና እረስ በእርስ የመሰማማት ስሜት አሳልፈናል፤ አንገታችንን ሊያሰደፋ ከተሸረበብን የእምነት ነጠቃ ሴራ በማምለጥ ከምን ግዜውም በተለየ ቀጣዩ የትግል ተሰላፊ እኔን አድርገኝ በሚል ተማፅኖ አሳልፈናል፤ ዳግም ላናንሰራራ አከርካሪያችንን እንደመቱ በፎከሩብን ጠላቶቻችን ላይ ወሩ ባጎናፀፈን ትዕግስትና ፅናት ፉከራቸውን በማስታገስ አሳልፈናል፤ ‹‹እንግዲህ

ምን ይደረጋል›› ከሚሉት አጉል ብሂል በመውጣት የወሩ መገለጫ በሆነው የበላይነትና የአሸናፊነት ስሜት አሳልፈናል፡፡ አንዳንዶች በተሳሳተ መልኩ እንደተረዱት በእምነት ነፃነት እጦት አንገታችንን ደፍተን እያነባን ሳይሆን ለእምነት ነፃነት ያለንን ሁሉ ልንሰጥ እንደምንችል ለራሳችንም ለሌችም ማረጋገጫ በመስጠት አሳልፈናል፤ በውሃ ጥም የደረቀ ጉሮሮአችን ብሶት ባመነጨው ጨዋማ እምባችንን እያራስን ብቻ ሳይሆን አላህን በመማፀንና ለዲናችን ያለንን ፍቅር በማረጋገጥ ለወትሮው የደረቀው አይናችን እያነባ አሳልፈናል፤ በሌላም በሌላም ከወሩ ክብርና ሞገስ ጋር ከሚሄዱ መልካም መገለጫዎች ጋር በተሳሰረ መልኩ ወሩን አሳልፈናል፡፡ አሁን ደግሞ ዒድን ልናከብር እየተዘጋጀን እንገኛለን፡፡ አልሃምዱሊለላህ!!!

Thursday, August 16, 2012

ESAT Netsa Bihir Article from Esubalew Germay about muslims Ethiopia

“አወል አባ ፊጣ ከለቡ” ዒድ ሙባረክ ነው የሚባለው፡፡

አዲስ ዘመን በ “አጀንዳ/ደብዳቤዎች” አምድ ስር ዜጎች ነፃ አስተያየታቸውን የሚሰጡበት ነው በሚል በሐሙሱ የነሐሴ 10 2004 ዕትም የ “አወል አባ ፊጣ-ከለቡ”ን አስተያየት አስፍሯል፡፡
ረመዷን ሊሰናበተን ቢበዛ ሁለት ቀናት ብቻ በቀሩበት በዚህ ሰዓት “ሮመዳን ከሪም” ሲል የተመኘልን የ“ሮመዳን ለሰላም” ፅሁፍ አዘጋጅ ግለሰብ ከፅሁፉ ሁለት ነገሮችን አትርፏል፡፡ የመጀመሪያው ልምድ ያለው ፀሐፊ መሆኑን የሚመሰክር መጣጥፍ ማዘጋጀቱን ሲሆን ሁለተኛው ደግሞ የቀለጠ የኢ.ሕ.አ.ዴ.ግ ካድሬ መሆኑን ማስመስከሩ ናቸው፡፡ ጉዳዩ ወቅታዊ እና መቋጫ ያልተበጀለት ሐቅ ከመሆኑ ጋር በቀር አምዱን ካፍ እስከ ገደፉ የሞሉት ቃላት በጌታዬ ስም እምላለሁኝ ፍፁም ከእውነት የራቁ እና ለፕሮፓጋንዳ ፍጆታ ብቻ እንዲውሉ የተዘጋጁ ናቸው፡፡

Wednesday, August 15, 2012

አንድ ለአምስት ተደራጁበማለት ሊከውኑት የነበረው እንቅስቃሴ ባለፈው ቅዳሜና እሁድ በሙስሊሙ የነቃ ተቃውሞ ሙሉ በሙሉ ሊከሽፍ ችሏል፡፡

ድምፃችን ይሰማ
ትኩስ መረጃ
ሙስሊም ሆይ ይህን ጉድ ሰማህን፤ ላልሰማው አሰማ!!!
የፌዴራል ጉዳዮች ሚኒሰተር፤ የኢህአዴግ የድርጅት ጽ/ቤት እና የብሄራዊ ደህንነትኤጀንሲ የዒድን ሰላት ለማጨናገፍ ያለ የሌለ ኃይላችውን አሟጠው እየሰሩ መሆኑንየውስጥ ምንጮቻችን አስታወቁ፡፡ በጣም በሚገርም ሁኔታ ለዚህ ጉዳይ የመንግስትንመዋቅር ከመጠቀም አልፎ ሌላ ስራና ኃላፊነት የሌለባቸው እስኪመስል እያንዳንዱ የመንግሰት ቢሮ የራሱን አክሽን ፕላን አውጥቶ በመንቀሳቀስ ላይ ይገኛል፡፡ ለዚህም የአህለሱና ወል ጀማዓሱፊያ የሚባል የአህባሽ ማህበር በመላው አ/አበባ በማቋቋም ሰላማዊ ተቃውሞዋችንንለመግታት አስበው ባሳለፍንው ሳምንት በየሰፈሩ እየዞሩ አንድ ለአምስት ተደራጁበማለት ሊከውኑት የነበረው እንቅስቃሴ ባለፈው ቅዳሜና እሁድ በሙስሊሙ የነቃ ተቃውሞ ሙሉ በሙሉ ሊከሽፍ ችሏል፡፡ ለአብነት ያክል በኮ/ቀራንዮ ክ/ከተማ ዉስጥ ባሉት 15 ወረዳዎች የኢህአዴግ የየወረዳው ካድሬዎችና በበድኑ የሚንቀሳቀሰው መጅሊስ አባላት በተለይም የቃጥባሬው ሸኽ የልጅ ልጅ የሆኑትን ሙሪድ ሰዒድን በመጠቀም በየወረዳው አንድለአምስት ተደራጁ እና በህዝበ ሙስሊሙ ኮሚቴዎች ላይ አሸባሪ ናቸው አይወክሉንምብላችሁ ሰላማዊ ሰልፍ ውጡ በማለት ህዝቡን ለማደራጀት ያደረገው እንቅስቃሴ ፍጹም ሳይሳካ ቀርቶዋል፡፡‹‹ ልፋ ያለው ነጋዴ አያተርፍ›› እንዲሉ አሳዛኞቹ ‹‹ትንንሾቹ›› የኢህአዴግ ካድሬዎች የአለቆቻቸውን ትዕዛዝ ለማስፈጸም ሌሊት ሲዞሩ፤ ስብሰባ ሲጠሩ፤ አንድ ለአምስት ተደራጁ ሲሉ ቢከርሙም የነቃውን ሙስሊም ፍጹም ከአቋሙ ሊያንቀሳቅሱት አልቻሉም፤ አልሀምዱሊላህ!!! ይህ ተሳክቶ ቢሆን ኖሮ ከዒድ ሰላት በፊት እነዚህን አካላት በማስተባበር ሰልፍ እንዲወጡ በ
ማድረግና በዒዱ ቀን የተቃውሞ መልእክቶችን እንዲያስተላልፉና በህዝበ ሙስሊሙ መሃከል ግጭት እንዲፈጠር ለማድረግ ታስቦነበር፡፡ ይህም ሆኖ የኢስላም ጠላቶች ተኝተው አልተኙምና የወጠኑት አለመሳካቱን በመረዳት ሰላማዊ ተቃውሞዋችንንና የዒድን ሰላት ለማደናቀፍ ከላይ የጠቀስናቸው አካላት ማለትም የፌዴራል ጉዳዮች ሚኒሰተር፤ የኢህአዴግ የድርጅት ጽ/ቤት እና የብሄራዊ ደህንነት ኤጀንሲ የሚከተሉትን እቅዶች ነድፈው በመንቀሳቀስ ላይ ይገኛሉ፡፡
1ኛ) የፊታችን ጁሙዓ ሙስሊሙ ተቃውሞ ያደርጋል ብለው በማሰብ ባዘጋጃቸው የደህንነት አባላት እና የአህባሽ ቅጥረኞች በመስጂዱ ኢማም ላይ የድብደባ ወንጀል በመፈጸም ይህንን ተከትሎ ሊፈጠርየሚችለውን ችግር ተገን በማድረግ ብዙ ሰላማዊ ሙስሊሞችን ማሰርና ምናልባትም ጥቂቶችን በመግደል የዒዱን ሰላት በስታዲየም እንዳይሰገድ ማድረግ ፤ ከሂህበተጨማሪ በሙስሊሙ ላይ ፍርሃትን በመንዛት በመስጂድም ጭምር እንዳይሰገድ ማድረግ፡፡
2ኛ) የዒዱ ቀን ከመድረሱ አስቀድሞ ይንቀሳቀሳሉ ወይንም ተጽዕኖ ፈጣሪ ናቸውብሎ የሚያምናቸውን ግለሰቦች እያሳደዱ ማደን ፤ ይህንን ስራ የክልል ከተሞች ሳይቀሩ እንዲሰሩት ትእዛዝ የወጣ ሲሆን ከነዚህም መሃከል በአማራ ክልል በደሴ በባቲና በከሚሴ፤ በኦሮሚያ ክልል በበደሌኢሊባቡር ጅማና ወለጋ-ጊምቢ እንቅስቃሴዎች መጀመራቸውን ምንጮቻችን ገልጸዋል፡፡
3ኛ) የዒድ ሰላት የሚሰገድበትን ሰዓት ቀድሞ በሚዲያ በማስነገር ህብረተሰቡ ያንን ሰዓት አስቦ ስለሚመጣ ቀድሞ በጠዋት በትንሽ ጀማዓ በማሰገድ አንድነቱን መበተንና ህዝበ ሙስሊሙ ሰላቱአምልጦኛል ብሎ ወደቤቱ እንዲመለስ ማስገደድ
4ኛ) ወደ ስታዲየም የሚጓዘው ህዝበ ሙስሊም ላይ የተለያዩ እክሎችን በመፈጸምወደ ብስጭት መምራት፡ ከዚህ መሃከል ብዙ መኪናዎችን እንደተበላሹና እንደተጋጩ በማስመሰል አውራ ጎዳናዎቹን መሙላትና መተላለፊያ መንገድ ማሳጣት፤ የመኪና ፓርኪንግ የለም በማለት በጠዋት ወደ ቦታው የሚሄደውን ህዝበ ሙስሊም እንዲጉላላ ማድረግ
5ኛ) በስታዲየም ዙሪያ ያሉትን ማይክራፎኖች እና ስፒከሮች እንዳይሰሩ በማድረግ ለህዝቡ ድምጽ እንዳይደርስ ማድረግ
6ኛ) በቃጥባሬ ጀመዓ ስም እና በኑር(በኒ) መስጂድ ምክትል ኢማም የሚነበቡ የህዝበ ሙስሊሙን ኮሚቴዎች የሚያወግዙ ግጥሞችን ማስነበብና ከየሰፈሩ ለተመረጡ ህጻናት ከበሮና ድቤ በማስያዝ መጅሊስንና መንግስትን የሚያወድስ ግጥሞችንና መንዙማዎችን በማስባል በህዝበ ሙሰሊሙ መሃከል ጸብ እንዲፈጠር ማድረግ ይህ ባይሳካ እንኳን የትክክለኛው ሙስሊም አቋም ይህ ነው በማለት ለተለመደው የሚዲያ ፍጆታቸው ግብዓት ማደረግ
7ኛ) በዒድ ሰላት ወቅት ከፍተኛ ቁጥር ያለውን ከባባድ መሳሪያ ያነገቡ የመከላከያ ሰራዊት አባላቶችን በአውራ ጎዳናዎች ላይ በማሰማራት በህዝበ ሙስሊሙላይ ፍርሃትና ሽብር መንዛት ሲሆኑ ይህንን ተግባራዊ ለማድረግ ከፍተኛ እንቅስቃሴ በማድረግ ላይ ይገኛሉ፡፡ ይህንን የተከበረው ህዝበ ሙስሊም በመረዳት የተለመደ ሰላማዊነቱን እና ህገመንግስታዊነቱን በመጠበቅ መረጃውን ለመላው ሙስሊም ያስተላልፍ ዘንድ እናሳስባለን፡፡
‹‹ወመከሩ ወመከሩላሃ፤ ወላሁ ኸይሩል ማኪሪን!››!!!

መንግስት የገዛ ዜጎቹን ለማሠርና ለማጋጨት ቀን ከሌት ሲደክም የሐሰት ክስ ሲያቀርብ ኢትዮጵያ ብቸኛዋ ሳትሆን አትቀርም፡፡

ጥያቄያችንን ከስምንት ወር በላይ ፍጹም ሰላማዊ በሆነ መልኩ ስናቀርብ ቆይተናል፡፡ ታላላቅ የዓለማችን ኢንሳይክሎፒዲያዎችና መዝገበ-ቃላት ሰላማዊ ትግልን ‹‹ከዜጎች ፍላጎት ተቃራኒ የሆነ ህግን ወይም ስርዓትን ለመቃወም ወይም ለማስወገድ የሚደረግ ሁከት አልባ ንቅናቄ›› ሲሉ ይገልጡታል፡፡ በዚህ ረገድ የኛ ንቅናቄ መነሻው ‹‹በሕገ-መንግስቱና በሌሎችም የሃገሪቱ ህጎች ላይ የሠፈሩ ድንጋጌዎች ይከበሩ›› የሚል እንጂ ‹‹የተደነገገ ሕግ ይጣስ ወይም ይሰረዝ አልያም ስርኣቱ ይቀየር›› የሚል ባለመሆኑ እስከዛሬ በዓለማችን ከታዩት ሠላማዊ ትግሎች ይለያል ብለን እንገምታለን፡፡ በዓለም ላይ ዜጎች መንግስትን ‹‹ህገ-መንግስቱን አክብር›› ብለው ለወራት ሲደክሙ፣ ሲታሠሩ፣ ሲሰደዱና ሲሰቃዩ የኛው የመጀመሪያው ሳይሆን አይቀርም፡፡

http://www.hrw.org/news/2012/08/15/ethiopia-prominent-muslims-detained-crackdown

(Nairobi) – The Ethiopian government should immediately release 17 prominent Muslim leaders arrested as part of a brutal crackdown on peaceful Muslim protesters in Addis Ababa, Human Rights Watch said today. A court is expected to rule during the week of August 13, 2012, on whether to bring charges against the detainees who have been held for almost three weeks in a notorious prison without access to lawyers.

August 17, 2012 Jumaa Prayer Noice


የፊታችን ጁምአ የኢድ ዎዜማ በመሆኑ ማንኛዉም አይነት ተቃዉሞ በሁሉም ቦታዎች መኖር እንደሌለበት ስለታመነበት ማንኛዉም አይነት ተቃዉሞ መደረግ እንደሌለበት እናስታዉቃለን:: ምክንያቱም የፊታችን ጁምአ መንግስት የኢድ ሰላትን ለማጨናገፍ ያመቸዉ ዘንድ የተለያዩ ሴራዎችን ማሴሩን በተጨባጭ ተደርሶበታል:: ከጁምአ ሰላት ቡሃላ ህዝበ ሙስሊሙ በተለያዩ ከተሞች በሚገኙ መስጂዶች በሰላማዊ መንገድ ተቃዉሞዉን ሲያሰማ የነበረ ሲሆን መንግስትም ይህንን ተቃዉሞ ተገን በማድረግ ረብሻ በመፍጠር የኢድ ሰላታችንን ተሰብስበን እንዳንሰግድ ለማድረግ ስላሰቡ ይህንን ሴራቸዉን ለማክሸፍ ሲባል የፊታችን ጁምአ በመላዉ ሀገሪቱ ሙስሊሙ ማህበረሰብ በዝምታ ያሳልፈዉ ዘንድ እናሳስባለን:: ማንኛዉም አይነት የዝምታም ሆነ ሌላ ተቃዉሟችንን የሚገልፁ ነገሮችን ማድረግ እንደማይገባን እናሳስባለን:: በታላቁ አንዎር መስጅድም ተቃዉሞ የሚደረግ ከሆነ የመስጂዱን ኢማም በግርግር ለመደብደብና ጥቂት አክራሪዎች ጥቃቱን ፈፀሙት በማለት በሙስሊሙ ላይ በማላከከ የኢድ ሰላትን በጀምአ በአንድ ቦታ እንዳይሰገድ ለማድረግ እንዳማራጭ ዘዴ ስለያዙ በታላቁ አንዎር መስጂድም ምንም አይነት ተቃዉሞ መደረግ እንደሌለበት እናሳስባለን:: ህዝበ ሙስሊሙም በየመኖሪያ አካባቢዎች በሚገኙ መስጂዶች የጁምአን ሰላት ይሰግድ ዘንድ እናሳስባለን:: በአንዎር መስጂድ በብዛት ሆነን መስገዳችን ተቃዉሞ ባናሰማም በህዝቡ ቁጥር ተገን በማድረግ አላማቸዉን ለማሳካት የተለያዩ ሴራዎችን ሊያሴሩ ስለሚችሉ አብዛኞቻችን ከረመዳን በፊት ስንሰግድባቸዉ በነበሩ መስጂዶች የጁምአን ሰላት መስገድ እንደሚኖርብን እናሳስባለን!! ይህንን መልዕክት በተለያዩ መንገዶች አስተላልፍ!!! "ብልጦች አይደለንም ብልጣብልጦችም አያታልሉንም"

Tuesday, August 14, 2012

የ Google+ page የከፈተ ሲሆን የ“ድምጻችን ይሰማ


ፌስቡክ ሙስሊሙ ህብረተሰብ እየደረሰብትን ያለውን የመብት ረገጣ ለህብረተሰቡ ከማሳወቅ አንጻር ያለውን ጉልህ ሚና ለማጨናገፍ አንዳንድ ባለስልጣናት እንዲዘጋ እየጠየቁ መሆኑን ማወቅ ተችሏል፡፡ ይህ እኩይ ዐላማቸው ተሳካላቸውም አልተሳካላችው አማራጭ መረጃ መለዋወጫ ዘዴ ዎችን አዘጋጅቶ መቀመጥ ብልህነት ነው፡፡ ከዚህ አንጻር “ድምጻችን ይሰማ” አስተማማኝ የሆነ ቀጣይነት እንዲኖረውና በፌስቡክና ትዊተር ብቻ ተወስኖ እንዳይቀር ተመሳሳይ አገልግሎት የሚሰጥ የ Google+ page የከፈተ ሲሆን የ“ድምጻችን ይሰማ” ተከታታዮች የነበራችሁ ሁሉ የዚህ አገልግሎት ተጠቃሚ ለመሆን ከወዲሁ የፔጁ አባል እንድትሆኑ እናሳስባለን፡፡ Google+ ከዚህ ቀደም ላልተጠቀማችሁ እንዴት አባል መሆን እንደምትችሉ ከዚህ በታች ባጭሩ ተቀምጧል፡፡ 1. የጉግል አካውንት ከሌሎት ይክፈቱ 2. https://gplus.is/DimtsachinYisema ወይም https://plus.google.com/100427562987310232548/posts የሚለውን ሊንክ ይክፈቱ 3. ከዚህ ቀደም Google+ ተጠቅመው የማያውቁ ከሆነ ከዚህ ጽሁፍ ጋር በተያያዘው አነደኛ ምስል ላይ እንደሚያዩት Join Google+ የሚለውን አይከን ይጫኑ፡፡ ከዚያም በሁለተኛው ምስል ላይ እንደሚታየው Upgrade የሚለውን ይጫኑ፡፡ አሁን የGoogle+ ተጠቃሚ ለመሆን ተመዝግበዋል ማለት ነው፡፡ 4. በመቀጠል ከላይ የተቀመጠውን https://gplus.is/DimtsachinYisema ወይም https://plus.google.com/100427562987310232548/posts ሊንክ ሲጫኑ የ“ድምጻችን ይሰማ” ገጽ በሶስተኛው ምስል ላይ እንደሚታየው ይመጣል፡፡ የ“ድምጻችን ይሰማ” ተከታታይ ለመሆን በምስሉ ላይ እንደሚታየው Follow የሚለውን ይጫኑ፡፡ ከዚያም በአራተኛው ምስል ላይ እንደሚታየው Following የሚለው ላይ ምልክት ያድርጉ፡፡ ይህን ሲጨርሱ በአምስተኛው ምስል እንደሚታየው Following የሚል ጽሁፍ ከመጣ የ“ድምጻችን ይሰማ” የ Google+ page ተከታታይ ሆነዋል ማለት ነው፡፡ በቀጣይነትም እንደ አማራጭ የተያዙ ተጨማሪ የመረጃ መለዋወጫ መንገዶችን የምናስተዋውቃችሁ ሲሆን እስከዛው ሁላችንም የ“ድምጻችን ይሰማ” የ Google+ page ተከታታይ መሆናችንን እንድናረጋግጥ አደራ እንላለን፡፡ የ“ድምጻችን ይሰማ” የ Google+ page ተከታታይ ይሁኑ (5 photos)

The Truth On Ethiopian Muslims Struggle WATCH IT! YouTube


Monday, August 13, 2012

የወያኔ ጦር በአንደኛ ደርጃ ተጠንቀቅ እንዲዘጋጅ ተዛዝ ተላለፈ ።

የወያኔ ጦር በአንደኛ ደርጃ ተጠንቀቅ እንዲዘጋጅ ተዛዝ ተላለፈ ።
Facebook

ከቅርብ ግዜ ወዲህ የወያኔው ቡድን በኢትዮጵያውያን ሙስሊም ወገኖቻችን ሃይማኖት ጣልቃ መግባቱን ተከትሎ ህገመንግስታዊ መብታቸው እንዲከበር ድምጻችን ይሰማ በሚል መሪ መፈክር በአንድነት በረቀቀ እና በተደራጀ መልኩ ሰላማዊ ትግል በማካሄድ ላይ መሆናቸው ይታወቃል። ይህ በመላው ሀገሪቱ ስር የሰደደው የሙስሊሙ ተቃውሞ የወያኔ ተራ ማስፈራሪያ እና ዛቻ ሳይበግረው ከእለት እለት በመላ ሀገሪቱ እንደ ሰደድ እሳት ተቀጣጥሎ ለውያኔ እራስ ምታት እየሆነበት መምጣቱ የማይካድ ሃቅ ነው።

ጥላውን የማያምነው ወያኔ የነብርን ጭራ ከያዙ አይለቁ ከለቀቁ ? ነገር ሆኖበት የሃገሪቱን ጦር በአንደኛ ተጠንቀቅ ከማሰማራት አንስቷ ህዝበ ሙስሊሙ ኢትዮጵያዊ ወገናችን ላይ የጀመረው አስቃቂ የግድያ እና የአፈና ዘመቻ በቅርቡ አለማችንን ጉድ ካሰኘው ከበርማ ሙስሊሞች ዘግናኝ ድርጊት የከፋ ሊሆን እንደ ሚችል መጤውን የወያኔን ቡድን ማንነት ጠንቕቀው የሚያወቁ ኢትዮጵያውያን ውስጥ፡አዎቂ ምንጮች ይገልጻሉ።

እነዚህ ምንጮች በየወያኔ ስረአት ውስጥ በተፈጠረ የስልጣን ሽኩቻ ቡድኑ መፈረካከስ መጀመሩን በመግለጽ፡ የኢትዮጵያ ህዝብ እና ሰራዊት ይህን በጭቁኑ ወገናችን የትግራይ ህዝብ ስም የሚነግደውን አናሳ የወያኔ ቡድን ነትሎ በመምታት ከሰፊው ህዝባችን ጫንቃ አሽቀንጥሮ ለመጣል ህዝበ ሙስሊሙ ወገናችን የጀመረውን የሃይማኖት ጥያቄ በመቀላቀል ወደ አጠቃላይ የመብት ጥያቄ ትግሉን በማሸጋገር የዚህን ቡድን ስረአት ቀብር ማረጋገጥ፡ እንደ ሚጠበቅብን አበክረው መክረዋል።

ከዚህ በታች በደሴ ሙስሊም ወገናችን ላይ ያለፈው የጁመአ ጸሎት ስረአት በወያኔው አናሳ ቡድን የአጋዚን ጦር የተፈጸመው አስቃቂ ግፍ መሆኑንን እንገልሳለን ።

በሳውዲ አረቢያ የሪያድ እና አካባቢው ኢትዮጵያውያን ወጣቶች ማህበር

ይድረስ ለውድ ኮሚቴዎቻችን

ዛሬን ጨምሮ ባሳለፍናቸው አራት የረመዳን ጁመዓዎች የኢትዮጵያ ሙስሊም የደረሰበትን የብስለትና የአይበገሬነት ደረጃ በሺዎች የሚቆጠሩ ወንድምና እህቶቻችን ታስረው በመቶዎች የሚቆጠሩቱ ደግሞ ተደብድበው ነገር ግን የበለጠ ትግላችን ተጠናክሮ ለትግል ታሪካችን ድንቅ ምእራፍ ጨምረንለታል፡፡ ህዝበ ሙስሊሙ ፍፁም ሰላማዊ በዲኑ ለመጡበት ደግሞ ቅንጣት የማይደራደርና ለዲኑ እስከመጨረሻው ዘብ እንደሚቆም በድጋሚ አሳይቷል፡፡ ጌታችን አላህ በቁርዓኑ ‹‹የአላህን ብርሀን በአፎቻቸው ሊያጠፉ ይከጅላሉ አላህ ግን ዲኑን መሙላት እንጂ እንቢ ይላቸዋል›› አይደል ያለን፡፡ እኛ የአላህ ባሮች ነን ጌታችን ደግሞ አላህ ነው፡፡ አላህ ታላቅ ነው!! አላሁ አክበር!! እያልን ለዲናችን መከበር ዘብ እንቆማለን!! ለመብታችን እስከ መጨረሻው ፀንተን እንታገላለን!! አላሁ አክበር!! አላህ ታላቅ ነው!!
ለመንደርደሪያ ይህንን አልን እንጂ ዛሬ የምናካፍላችሁ ምናልባት የብዙዎቻችንንትርታ ያደመጠ ነው ብለን ያሰበነውን ለውድ ኮሚቴዎቻችን የተፃፈ አንድ ደብዳቤ ነው፡፡ እስኪ እናንተም የልችሁን ፃፉ፡፡ ኢንሻአላህ አንድ ቀን በመድብል ተዘጋጅቶ ይደርሳቸዋል፡፡ መልካም ንባብ፡፡

Friday, August 10, 2012

Video


Ethiopian authorities crack down on Muslim press

Nairobi, August 9, 2012--Ethiopian authorities must release a journalist who has been detained for almost three weeks, and allow three Muslim news outlets to resume publishing immediately, the Committee to Protect Journalists said today. Local journalists believe the Muslim press in Ethiopia is being targeted for its coverage of protests by the Muslim community.

Peacefull Struggle of Ethiopian Muslims

Yetafenu dimtsoch (Documentary Peaceful Struggle of Ethiopian Muslims)

 

Thursday, August 9, 2012

A Atatement From The World Federation of Muslim Scholars

አለም አቀፍ የሙስሊም ዑለማ አንድነት ማህበር በኢትዩጵያ መንግስት አማካኝነት እየተካሄደ ያለውን የሰብአዊ መብት ጥሰትን የሚያወግዝ መግለጫ አወጣ
 አዲስ አበባ  ሬዲዮ ቢላል ሐምሌ 3/2004
  በመግለጫውም መንግስት ኢትዩጵያውያን ሙስሊሞች ላይ እየፈጸመ ያለውን የሰብዓዊ መብት ጥሰትን ማቆም እንዳለበትና ችግሩን ከሙስሊሙ አመራር ጋር በመወያየት መፍታት እንዳለበት አሳስቧል ።
ይህ ካልሆነ ግን አገሪቷ ላይ የከፋ ክስተት ሊያስከትል እንደሚችልም አስጠንቅቋል። በተጨማሪም በአለም ላይ ያሉ ሙስሊሞች ግፍና በደል እየደረሰባቸው ያሉትን ሙስሊሞች በሙል ሊታደጓቸውና ከጎናቸው ሊሆኑ እንደሚገባም አሳስቧል።
ሙሉ መግለጫውን  እንደሚከተለው አቅርበነዋል :
“ ምስጋና ለአላህ ይገባው ፣ የአላህ እዝነትና ሰላም በመልክተኛው ሙሃመድ ፣ በባልደረቦቹ እና እነሱን በተወዳጁ ላይ ይሁን ። በመቀጠል ፡
ማህበሩ በ ኢትዩጵያውያን ሙስሊሞች ላይ እየተከሰተ ያለውን ድርጊት በንቃት እየተከታተለ ይገኛል።
ኢትዩጵያ የመጀመርያዋ ሙስሊሞች የተሰደዱባት፣ በታላቁ ነብዩ ሙሃመድ (ሰዐወ) አንደበት “እርሱ ዘንድ ማንም አይበደልም” የተባለለት የንጉስ ነጃሺ ሃገር ናት ። ነጃሺ የነብዩ ሙሃመድ (ሰዐወ) ባልደረቦችን  ይደርስባቸው ከነበረ ጭቆናና በደል የታደገ ታላቅ ንጉስ ነበር ።
ይህ በእንዲህ እንዳለ የኢትዩጵያውያን ሙስሊሞች ሁኔታ ከሃይለስላሴ ጀምሮ ወደከፋ አቅጣጫ ነበር ያመራው ። ሃይለስላሴ የኢትዩጵያውያን ሙስሊሞችን ጨቁኗል። የበደልን ገፈት አቅምሷቸዋል! ።
አሁኑ የአገዛዝ ስርአት ውስጥ ኢትዩጵያውያን ሙስሊሞች ሰብአዊ መብታቸውን ሙሉ በሙሉ ባይጎናጸፉም በአንጻራዊ መልኩ ግን የነጻነት ጎህ በትንሹም ቢሆን አፈንጥቆላቸዋል።
ሰሞኑን ትልቅና አስደንጋጭ ክስተት ተከስቷል እርሱም የመንግስት ሃይላት አሸባሪ እና አልቃኢዳ በሚል ተልካሻ ምክንያት ዱዓቶች እና ሃይማኖተኛ ወጣቶች ላይ ከፍተኛ የሆነ ጥቃት ሰንዝሯል፣ በመቶዎች የሚቆጠሩትም በየ እስር ቤቶች ታጉረው ስቃይና ግርፋት እየተፈጸመባቸው ይገኛሉ ፣ መሳጂዶቻቸው ተደፍረዋል፣  ጋዜጦቻቸውና መጽሄቶቻቸውም ታግደው ይገኛሉ። ከተጠቀሱት በላይ አስከፊው ድርጊት ደግሞ መንግስት  በሃይልና መጅሊስን በመጠቀም ጠማማው አብደላ አል_ሃረሪ ያመጣውን የአህባሽ እምነት ለማስፋፋት መዳከሩና በሙስሊሞች መሃከል ግጭትና እልቂት በመፍጠር የመንግስትን ፖለቲካዊ አላማን ለማሳካት የሚደረገው ጥረት ነው ።
ይህ ክስተት የኢትዩጵያውያንን ሙስሊሞች ቁጣ የቀሰቀሰና ታላቅ የሆነን ተቃውሞ ያስነሳ ክስተት ነው።
ይህ መከራና ችግር በኢትዩጵያውያን ሙስሊሞች ላይ ሰፍሮ ባለበት ሂደት አለም አቀፍ የሙስሊም ዑለማዎች አንድነት ማህበር በጉዳዩ ላይ ያለውን ዓቋም በአጽንኦት እንደሚከተለው ያሳውቃል፡
1_ ማህበሩ የኢትዩጵያ መንግስት በሙስሊሞች ላይ እያደረሰ ያለውን በደል እንዲያነሳ፣ሃይማኖታዊ ነጻነታቸውንና ተወካዩቻቸውን በራሳቸው የመምረጥ መብታቸውን እንዲያከብር በተጨማሪም ከክርስትያኖች ጋር እኩል መብታቸውንና ግዴታቸውን ማረጋገጥ እንዲችሉ ማድረግ እንዳለበት ያሳስባል ። 
ኢትዩጵያውያን ሙስሊሞች  ሃገራዊ ግዴታቸውን እየተወጡና ብዙሃን ሆነው ሳለ ለምንድነው መብታቸው የሚረገጠው !? በክልሎቻቸው ላይስ ለምንድነው ድህነት፣መሃይምነትና ኋላቀርነት እንዲንሰራፋ የሚደረገው!?።
  ኢትዩጵያውያን ሙስሊሞች በታሪክ ሂደት ላይ የመቻቻልና የአብሮነትን ባህል ያሳዩ ናቸው። ያለምንም ጥርጥር የኢትዩጵያን መንግስትና ህዝቦቿን  ጠንካራ ሊያደርግ የሚችለው መብትንና ግዴታን በእኩልነት መወጣት ሲቻል ብቻ ነው።
2_ አምባገነንት፣እስራት፣ግርፋት፣ያለምንም መረጃ ሙስሊሙን መወንጀል እንዲሁም በመሃከላቸው ግጭትንና ረብሻን ማቀጣጠል ፡ በፖለቲካዊ ሂደት ላይ በሀገሪቷ ላይ ውድመትንና ህዝባዊ እልቂትን ከማስከተል ውጭ ውጤታማ እንዳልሆነ በሶማልያና መሰል አገሮች ላይ ዓለም በሙል በገሃድ ያየው ነው። ስለዚህ  የኢትዩጵያ መንግስት ችግሩን ከሙስሊሙ ምሁራን ተወካዩችና ከጎሳ ባላባቶች ጋር በመደራደር መብትንና ተቻችሎ መኖርን ዘላቂ በሆነ መልኩ ሊያረጋግጡ በሚችል መልኩ ችግሩን መፍታት አለበት።
3_ ማህበሩ ዓለም አቀፍ ኢስላማዊ መረዳጃ ማህር፣ የሙስሊም ምሁራንና ልሂቃን ባጠቃላይ በአለም ላይ ላለው ሙስሊሙ ማህበረሰብ ከኢትዩጵያውያን ሙስሊም ወንድሞቻቸው ጋር በመሆን ማቴርያላዊም ሆነ መንፈሳዊ ድጋፍ እንዲያደርጉላቸው ጥሪውን ያስተላልፋል።
4_ ማህበሩ ለአለምአቀፍ መረዳጃ ማህበራትና አለምአቀፍ ሰብዓዊ ድርጅቶች  ለኢትዩጵያውያን ሙስሊሞች ልዩ ትኩረት እንዲሰጡና የተለያዩ ዘርፎችን ያማከለ እድገት እንዲፈጠር የበኩላቸውን አስተዋጽኦ እንዲያደርጉ ጥሪ ያቀርባል።
5_ ማህበሩ በሊቀመንበሩ መሪነትና በታላላቅ ልዑካኖቹ አማካኝነት ኢትዩጵያውያን ሙስሊሞች ያሉበትን ነባራዊ ሁኔታ ለማወቅና ከኢትዩጵያ መንግስት እንዲሁም ከሙስሊሙ ምሁራን ጋር ውይይት ለማድረግ ኢትዩጵያን ለመጎብኘት ዝግጁ መሆኑን ያሳውቃል ።
በመጨረሻም  የማህበሩ ፍላጎት በ ኢትዩጵያ ሰላም፣መቻቻል፣እኩልነት፣ፍትህ እና ሁለገብ የሆነ እድገት ሰፍኖ ማየት መሆኑን እናሳቃለን።
“በላቸውም፦ስሩ አላህ ስራችሁን በእርግጥ ያያልና መልእክተኛውና ምእመናንም (እንደዚሁ ያያሉ) “ (አል_ተውባ: 105)

ደውሃ ረመዳን 18/1433 እንደ ሂጅራ አቆጣጠር
ወይም እአአ 06/08/2012
ፕር/ዩሱፍ አልቀርዳዊ  የማህበሩ ሊቀመንበር
ፕር/አሊ አል_ቁራ ዳጊ የማህበሩ ፕሬዝዳንት
The World Federation of Muslim Scholars issued a statement calling on the Ethiopian government to protect the rights of Muslims and dialogue with their leaders, and warned the consequences of causing discord among them, also called the Islamic world to protect their fellow oppressed everywhere, and this is the text of the statement:

ሰላማዊና ደማቁ ተቃውሞአችን በአሁኑ ጁምዓም ይቀጥላል Friday August 9, 2012



ከታች የተዘረዘሩት የነገ ጁምአ የተቃዉሞ ሂደታችን ፍፁም ሰላማዊ ሆኖ መጠናቀቅ ስላለበት የጁምአ ሰላት ከተጠናቀቀ ቡሀላ ሁላችንም ባለንበት ቦታ በመቀመጥ ብቻ ነዉ ሰላማዊ የተቃዉሞ ድምፃችንን የምናሰማዉ:: ባለንበት ቦታ ተቀምጠን ተቃዉሟችንን መግለፃችን ማንኛዉም አካል ሰላማዊ ሂደታችንን ለማደፍረስ ቀዳዳ እንዳያገኝ ያደርገዎል:: ከጁምአ ሰላት ቡሀላ ሁሉም ሰዉ በቦታዉ መቀመጡን እርግጠኛ እንሁን!!! ማንኛዉም ሰዉ ከመቀመጫዉ ተነስቶ እንቅስቃሴ ሲያደርግ ከተመለከትነዉ ከዚህ ተግባሩ እንዲታቀብና እንዲቀመጥ ማድረግ ይኖርብናል:: ሌላዉ ማሳሰቢያ ተቃዉሟችንን በሰላማዊ መንገድ የምናካሂደዉ
አዲስ ዘመን ጋዜጣ በዕለተ ረቡዕ ነሐሴ 2 2004 ዕትሙ “የእስልምና ምክር ቤት አባላትን በአዲስ የመተካት መብት የሕዝበ ሙስሊሙ ብቻ ነው ” በሚል ርዕስ የኢትዮጵያ “ኡለማዎች” ምክር ቤት አስገነዘበ ሲል ስለ “ምርጫው”ሁኔታ ዜና ሰርቷል፡፡